አሸባሪው ማን ነው? ከተስፋዬ ዘነበ

ከሳምንታት በፊት በልእለሀያሏ አሜሪካ በቦስተን ከተማ የደረሰውን በአሸባሪዎች ጥቃት ህይወታቸውን ላጡና ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው የሃገሪቱ ዜጎች በህዝብ ይሁንታ ስልጣን ላይ ያሉት ፕሬዘዳንት ባራክ ኦባማ በሰላማዊ ህዝብ ላይ ለደረሰው አደጋ ሀዘናቸውን ለመግለፅና የወንጀሉን ፈፃሚዎች በቁጥጥር ስር ለማዋል መመሪያ ሲሰጡ ሰዓታት እንዳልወሰደባቸው ስንመለከት ወራት አልተቆጠረም፡፡በመሰረቱ ይህንን ዘግናኝ ጥቃት የፈፀሙት ፅንፈኛ አክራሪዎች ብዙም ሳይቆዩ በሃገሪቱ የፀጥታ ሃይሎች ታድነው በአጭር ጊዜ ውስጥ መያዛቸው ለሕዝቡ ታማኝ የሆነ መንግስት ዜጎቹን ከጥቃት ለመታደግ ምን ያህል እረፍት እንደሌለው የሚያመላክት ነው፡፡
ከላይ እንደመነሻ ያነሳሁት ሃሳብ ለዛሬው ፅሁፌ እንደ መንደርደሪያ እንዲረዳኝ እንጂ እውነተኛው የዲሞክራሲያዊ ስርዓት አራማጆች ለዜጎቻችቸው የሚሰጡት ክብር የሚሳት ሆኖ አይደለው፡፡ ይቀጥሉ…

አጀንዳ! ፍ.አ

አፄ ኃይለ ሥላሴ፣ ኢትዮጵያና የአፍሪካ አንድነት/ኅብረት በፍቅር ለይኩን

‹‹ኢንሳክሎፒዲያ ብሪታኒካ›› ስለ አፄ ኃ/ሥላሴ ባቀረበው አጠር ያለ ጽሑፍ እንዲህ ብሏል፡- ‹‹Haile Selassie played a very important role in the establishment of the Organization of African Unity in 1963.››
ዕለታዊው የአዲስ ዘመን የወርኻ ግንቦት 15 ቀን 1955 ዓ.ም ዕትሙ በፊት ለፊት ገጽ ላይ፣ ‹‹ሠላሳ የአፍሪካ መሪዎች በተገኙበት ጉባኤ በአፍሪካ አዳራሽ ተከፈተ፡፡ ግርማዊ ጃንሆይም የጉባኤው የክብር ሊቀመንበር እንዲሆኑ ተመረጡ፡፡›› በሚል ዐቢይ ርዕስ ዜናና ሰፊ ሐተታን ይዞ ወጥቶ ነበር፡፡ ይቀጥሉ…

ከሙስናው በስተጀርባ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

May 15th, 2013

በሕወሐት የተፈጠረው የቀውስ ማእበል አድማሱን እየለጠጠ መሔዱን ተከትሎ «ታማኝ» ሆነው በሙስና ሲያገለግሉ የቆዩትን ጭምር እየበላ እንደሚገኝ የቅርብ ምንጮች አስታወቁ። በቀዳሚነት የሚያነሱት በጉምሩክ ቁልፍ ስልጣን የነበረውን የሕወሐት አባል ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስን ሲሆን እንዴትና በማን ወደስልጣን እንደመጣ እንዲሁም ምን-ምን ተግባራት ይፈፅምና ያስፈፅም እንደነበረ ምንጮቹ ሂደቱን እንደሚከተለው ይገልፁታል። ይቀጥሉ…

አምባገነንነት ሲለመልም ነጻ ፕሬስ ይጠወልጋል በታሪኩ አባዳማ

May 13th, 2013

ተገፊዎች የባህሪ ለውጥ ኣምጡ እንጂ! ገለታው ዘለቀ

May 13th, 2013

ልትታተም ካሰበች ኣንዲት ልቦለድ ጽሁፍ ላይ ኣንድ የምናብ ሰው ከተገረመበት ነገር ተነስተን ኣጭር መልእክት ለማቀበል እንሞክራለን። ይህ የምናብ ሰው ወደ ኣንድ ሃገር ይሄድና በዚያ በኣንድ ሆቴል ውስጥ ተቀምጦ ናሽናል ጂኦግራፊ የተሰኘውን የ ቴሌቪዥን ፕሮግራም ያያል። በወቅቱ ይተላለፍ የነበረው ፕሮግራም የዱር እንስሶች ኑሮ ነው። ይህ የምናብ ሰው ከኣልጋው ጫፍ ላይ ቁጢጥ ብሎ ረጃጅም ጢሙን ቁልቁል እየላገ ይህን ፕሮግራም ያያል። የሚያማምሩ የሜዳ ኣህያዎች መንጋ ረጋ ብሎ ሳሩን ይግጣል። ጥቂት ሳይቆይ ከረጃጅሙ ሳር ውስጥ ሲሹለከለኩ የነበሩ ሶስት ጅቦች መጡ። ኣንዱን ጅብ ቀድሞ ያየው የሜዳ ኣህያ ሩጫውን ሲቀጥል ሌላው ነገሩ ያልገባው ሁሉ ተከትሎ ይሰግር ጀመር። ይቀጥሉ…

ዶ/ር አድሃኖም ስለሃገር ጥቅም ይከበር ብለው ያሉት ደስ ሲል ዓቢቹ ነጋ

May 13th, 2013

የኢትዮጵያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና ከጫካ ከመጡት የወያኔ ጀሌወች በትምህርትም ሆነ በአስተሳሰብ የተሻሉና በደም ያልተጨማለቁ ናቸው ሲባል ብዙ ሰምተናል። በመሆኑም ያስታርቂነትና የመልካም አስትዳደር ሚና ሊጫወቱ ይችሉ ይሆናል አያሉ ብዙ ሰውች ገምተው ነበር። አስተዋይና የምሁርነት ባህሪ እንዳላቸውም ይነገራል። ይቀጥሉ…

ያበቃለት ስርአት፤

May 10th, 2013

የሆሳዕና በዓል ለረዥም ዘመናት እየተመላለሰ በተከበረበት ዘመን ያልተከሰቱ በዘንድሮው ሆሳዕና ብቻ በወያኔ መንግሥት የተደረጉ አሰቃቂ ክስተቶች – ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

መግቢያ

በኢትዮጵያ ታሪክ በዓላቶቻችን፤ የገባር ወንዞችን ውሀ እያግበሰበሰ እንደሚጓዘው ዓባይ ወንዛችን፤ በወራት ታዝለው የኡደታቸውን ሂደት በመፈጸም ላይ ሳሉ የሚገጥሟቸውን ክስተቶች እየሰበሰቡ የሚቀጥሉ ናቸው። ክስተቶችም ደስታችንና ሀዘናችንን የምንገልጽባቸው ናቸው። ድርብ በዓላት የሚባል ስምም ተሰጥቷቸውል። ታሪካችንን ሰፊና ጥልቅ ያደረጉት፤ ስነ ጽሑፋችንንም ያዳበሩት አገራችን በዚህ መንገድ በመጓዝ የሰበሰሰበቻቸው ክስተቶች ናቸው። ከውጭ የሚመጣ ጠላትና ከውስጥም የጠላት ወኪል (የባንዳነት ውርስ የተሸከመ የባንዳ ልጅ) ሆኖ የሚሰለፈው መጀመሪያ የሚጋጭ ቀደም ብለው ከነበሩት ክስተቶችን ከተሸከሙት በዓላት ጋራ ነው። ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ፍኖተ ነጻነት እትም 74 ከዜናና ልዩ ልዩ መጣጥፍ ጋር