የሙስሊሞች ጉዳይ የኢትዮጵያ ጉዳይ! Jafar Hasen
ይህቺን አጭር ጽሑፍ ለመጻፍ ያነሳሳኝ ሚያዝያ 30 ቀን 2004 በፍኖተ ነፃነት ቁጥር 41 ላይ በቅርቡ የወጣው የሰለሞን ስዩም ጽሑፍና አያይዞም ለማጠናከሪያ ያቀረበው የቃለ መጠይቅ ድጋፍ ናቸው፡፡ ፍኖተ ነፃነቶች በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የሚያቀርቧቸው መረጃዎች ጥሩም አግባብም ያላቸው ናቸው፡፡ በብዛትም ሚዛን የያዙና ብዙዎችን የሚወክሉ ለአገርም ጥቅም የቆሙ ናቸው ለማለት ቅር አያሰኝም፡፡ ይቀጥሉ…
ከተገለጡት የተደበቁት ተሻሉ በታረቀኝ ሙጬ
ማሳሰቢያ፤ ይህ ጽሑፍ 4 ገጽ ከሩብ አካባቢ ነው፡፡ ረጂም ጽሑፍ ማንበብ እሚወዱ ብቻ እንዲያነቡት ይመከራል፤ ለስልቹዎች ስላልታሰበ በርዝማኔው ምክንያት አንዳችም ስድብ የማላስተናግድ መሆኔን ከወዲሁ አሳስባለሁ፡፡ ይቀጥሉ…
እስክንድር ነጋ በግሩም ተ/ሀይማኖት
ትግል ውጤቱ መራር እና ጣፋጭ ነው፡፡ ጣፋጩን ለማግኘት ከባዱን ጎዳና መጓዝ ግድ ይላል፡፡ እስክንድር ነጋ የታገለበትን ውጤት አዝመራውን አጭዷል፡፡ ከኢትዮጵያ ነፃ-ፕሬስ ጋር ከመጀመሪያው ጀምሮ የታገለ ጋዜጠኛ ነው፡፡ አሁን የወያኔ መንግስት ‹‹አሸባሪ›› የሚል ታፔላ ለጥፎለት በእስር ላይ ቢሆንም ድሉን ማጣጣም የቻለው የፔን ኢንተርናሽናል ሽልማትን ለማግኘት በመብቃቱ ነው፡፡ እሱ በእስር ላይ ቢሆንም ባለቤቱ እና የልጁ እናት ሰርክዓለም ፋሲል ሽልማቱን ተቀብላለች፡፡ እጅግ ደስ የሚል ዜና ስንሰማ ይህ የመጀመሪያችን አልነበረም፡፡ የኢትኦጵ ጋዜጣ አሳታሚ ሲሳይ አጌና አምና ተሸላሚ ነበር፡፡ መንግስት ‹‹አሸባሪ›› ይላል አለም ግን በስራቸው ሽልማት እንደሚገባቸው አምኖ ይሸልማቸዋል፡፡ አለም የተቀበለውን የማይቀበል፣ ሁሉ ያየውን የሚክድ ምን አይነት ቀጣፊ ብድን እንደሆን ኢትዮጵያን የሚያስተዳድራት ማወቅ አቅቷል፡፡ እንደ እስስት መልኩን እየቀያየረ እንደ እባብ ቆዳውን እየሸለቀቀ አጭበርብሮ ማለፍን ተግባሩ አድርጎታል፡፡ ይቀጥሉ…
ኢትዮጵያዊነትና አርበኝነት (ቅዱስ ሃብት በላቸው ከአድላይድ/ደቡብ አውስትራሊያ)
ስፍራው አዲስ አበባ፣ ዘመኑ 1931 ፋሺሽት ኢጣሊያ አገራችንን በሃይል በተቆጣጠረበት ወቅት ነው። አንድ ቀን የወራሪው ጦር አዛዥ የነበረው ማርሻል ባዶሊዮ ግራዚያኒ ሕዝቡን ለማታለልና ለመስበክ “በንጉሳችሁም ሆነ በኢጣሊያ ዘመን የተሰጣችሁ የክብር ልብስ ካለ ለብሳችሁ፤ የተሸለማችሁት ኒሻን ካለም ይህንኑ አድርጋችሁ ነገ ማለዳ ላይ ታላቁ ቤተ መንግስት እንድትሰበሰቡ!” ሲል አዲስ አበባ ውስጥ በራዲዮና በጥሩምባ ያስለፍፋል። ይቀጥሉ…

Recent Comments