አልቆርጥ አለ አንጀቴ - የምስራች ከአቡጊዳ

December 26th, 2009 ይመይሉ ይመይሉ ያትሙ ያትሙ

ጎኔ አላንቀላፋ
በቅሎ ስላላየሁ የዘራሁት ተስፋ
ስላልተመለስ ጥያቄየ የኔ
ወይ ፍንክች አጅሬ
ተስፋ አልቆርጥም እኔ ::

አውቃለው ሁሉንም
ለልጄም አንድ እናት
ለናቴም አንድ እኔ
ሁለቱም አይተኩኝ አያገኙም ሌላ
እነሱም አይችሉት ጸብ ከመጣ በኔ
ይግረማቸው እንጂ የራሴው ጭካኔ
በንባ እያጠብኩአቸው በልጦብኝ ወገኔ::

ይህም ብቻ አደለም ብዙ አይቱአል ይህ አይኔ
ፍትህ እስኪወለድ እምባ አርግዞ ሆዴ
ፀንቼ እጉአዛለሁ አያልቅም መንገዴ
ነፃ እስክንወጣ ካለንበት እስር
ምን አል ባይጠጣ ምን አል ባይጨፈር
ያሰብነው ተሳክቶ በደስታ እስክንሰክር::

እስኪ ልንገራችሁ አለኝ አንድ ሚስጥር
በታንክ ተከቦ ታጅቦ በወታደር
ለሊት ዘብ ተቁሞ ሲጠበቅ ዳር ድንበር
ግንቡና መሬቱ በሽጉጥ ሲታጠር
ፍራቻ አስጨንቆ እንቅልፍ ሲያሳጣ
የሰሩት ግፍ በቀል በህልም እየመጣ
ሲባንኑ ማደር በቅዥት ፈጣጣ
እሱ ነው እስር ቤት
ኡ ኡ ታ ለቅሶ የበዛበት ጣጣ::

እኔ ግን ነጻ ነኝ
ልክ እንደ ጲላጦስ
እጄን የታጠብኩኝ
ግን ፍትህ የጠማኝ የተንገበገብኩኝ
እውነቱን ልናገር እነሱም አልተዉኝ
እኔም አልተዋቸው
ነጻነት ሳይቀምሱ ከስር ሳልፈታቸው ::

የምስራች ከአቡጊዳ

  1. ይቻላል
    December 26th, 2009 at 22:22 | #1

    የምስራች እናመሰግናለን
    እንኳንም ይህንን ድምጽሽን ለመስማት አበቃን

    አዎን እነሱም ከተከኔቸሩብት ዪፈቱ:: እኛም አንተዋቸው
    እንደሻማ ቀልጣ የምታበራዋ የነጻነት ሻማችን ….

    እኔም አልተዋቸው
    ነጻነት ሳይቀምሱ ከስር ሳልፈታቸው ::

  2. ሳሚ
    December 27th, 2009 at 05:07 | #2

    የምስራች ጥሩ ብለሻል በግጥሙ; ብስለት የተሞላበት እውነት ነው የተናገሽው:: ባጣም እናመሰግናለን;;

አስተያየት መስጫው ተዘግቷል።