ዓባይ ደረቀ አሉ ! አሥራደው (ከፈረንሳይ)

December 11th, 2010 ይመይሉ ይመይሉ ያትሙ ያትሙ
  1. ጀንጀርበር
    | #1

    ለምንም አይደለም የተባሉ አስረዳው
    የማያውቅ ካለ እንግዲህ ይወቀው
    አባይ እንደሁሉም በትልቅነቱ
    መታወቅ አለበት ምንጩ መሰረቱ

  2. መሴ ሙለቱ
    | #2

    መርገመ በረከተን ማዳመጥ ካልቻለ፤
    ደረቀ ለመለመ ልዩነት የታለ፤
    ይድርቅ ዓባይ ካላጠጣ እናት፤
    የስም ማበሻ ሆኖ መርገመ በረከት፤
    መስማት ካልቻለ የደቻቱን ምሬት፤
    ምኑን ይሆናል የወንዞች ቅመ አያት፤
    የቱርኮች የግበጾች የፉከራ ክርፋቱ፤
    የወያኔ መዝሙር የማለዘን አዝማቹ፤
    የዉረደታችን ምንጭ የንብ አምራቹ፤
    መሆን ከመረጠ ምኑ ነዉ አባይነቱ፤
    እያድርን የማነሳችን የድንጋይነቱ፤
    የስደታችን መሰረት ጉድፈቻ ግኝቱ፤
    ባምቢሰን ላያሻግር ባዶ ጩኸቱ፤
    የመንጀር ጆሌ የወንጀለኛ ዳኛነቱ::

  3. ከንቲባው
    | #3

    ኣባይን ኣትመን ኣይምሰልህ ኣስሬ (ኣስራት)
    ደረቅሁኝ የሚልህ ሊያስወራህ ነው ወሬ

    አሱ ዙረታም ነው መጉዋዝ የለመደ
    በመሄድ የሾቀ በመሄድ ያበደ
    ለምሰር (ለግብጽ)ኮረዶች አንደተማገደ
    አናቱን ኣራቁቶ ለነሱ እንዳቀደ
    ጭዳ አንዳደረገን አኛን አንዳረደ
    ንስሃ ሳይገባ ስንት ኣመት ነጎደ?

    አሱ ኣታላይ ነው ኣይምሰልህ ኣስሬ (ኣስራት)
    ተናግሮ ሊያናግር ሊያስወራህ ነው ወሬ

    ኣባይ ኣለሌ ነው መረን የለቀቀ
    ኑብያን ከምስር አንዳፈራረቀ
    መታያ-አጅ መንሻ ሰብስቦ አንዳጨቀ
    አምዬን አናቱን አንዳመናጨቀ
    ጠላት አንዳፈካ ጠላት አንዳሳቀ
    አህት ወንድሞቹን ሁሌ አንዳስጨነቀ
    ንስሃ ሳይገባ ስንት ኣመት ኣለቀ?

    ኣባይ ‘ቁጭ-በሉ’ነው ኣይምሰልህ ኣስሬ (ኣስራት)
    ደረቅሁኝ የሚልህ ሊያስወራህ ነው ወሬ

  4. ከንቲባው
    | #4

    ኣስሬ (ኣስራት) ያልኩትን ኣስራደው በሚል ተክታችሁ ኣንብቡ

    ከምስጋና ጋር

  5. መሴ ሙለቱ
    | #5

    አኩርፈን ዉለን እንደገና አስልቅሶን:
    የቴዎድሮሱን ልጅ ከመቅደላ ገብረን:
    መይሳዉ የካሳዉን ይቅደምልን ብለን:
    በዮሃንሱ አንገት ቡራኬ ተለማምደን:
    ግብር መክፈላችንን ላናቆም ተማምለን:
    ቴዎድርስ ዳግማዊ ይህዉልህ ሽብሬን:
    አይሻ ዉቤትህ ተወባችነትዋን ነግርን:
    የለይኩኖ አምላክ ልጆች በምጥ ተይዘን:
    ከማልቀስ የተሻለ ሌላ ጉልበት አጥተን:
    ተከላካዩን ልጅ መስፍኔን አቁመን:
    ጫማ ስያስወልቁት በንዴት ግለን:
    ሜዳዉን አላወቅነዉ ጨዋታወም አልገባን:
    ብጫ አረንጉወዴ ቀይ የመቅደዳቸዉን:
    የእንተሎ እጅችዋን ማስታወቅያ አርገን:
    አባይ የጣናዉ ተባበረን ብለን ሰግደን:
    የአፍ መፍቻ መቀለጃ አደረጉን:
    ከመድረቅ ማዶ ውርደት ለሰነቀን:
    ይድረቅ አባይ ይትነን ምንጩን:
    ለቱርኮች ለግብጾች ለዉርደት ለዳረግን::

አስተያየት መስጫው ተዘግቷል።