የታሪክ፡ ተጠያቂወች፡ ሁነናል። ለጎሳዊ፡ ስነ፡ ልቦና፡ አናጎብድድ ክፍል፡ ሶስት፡ አክሎግ፡ ቢራራ (ዶር)

May 8th, 2012 ይመይሉ ይመይሉ ያትሙ ያትሙ
  1. በለው!
    | #1

    የኢትዮጵያን 11% ያላቋረጠ ተከታታይ ዕድገት የሚያወራው እንጂ ፊት ለፊት ቀርቦ በማስረጃ የሚያሳየን አልተገኘም:: አንዳንዶችም እንደበቀቀን የተወራን ደጋግሞ ከማውራት በቀር በቂ ግንዛቤ ያላቸው አደሉም”ተባለ አሉ” “ሰማሁ” “እንዳሉት” በተሰኙ ቅኔ ነገሮችን አጣፍጠው ሕዝብ ላይ ሲሞላፈጡ ይታያሉ::አብዛኛዎቹም እነ “ድንጋይ ብርቁ” እነ “መስተዋት ወርቁ” አውራጎዳና ሲያደንቁ በድንጋይ ክምር ፎቅ ሲመሰጡ ከታች የወደቁትን ድሆች ሲያናንቁ ይታያሉ::
    ሀገር የጋራ:የብሔር እኩልነት:የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት:የቋንቋ መብት: ማለት እራስን ከሌላው አግልሎ: ሳይግባቡ, መጣላት, መለያየት, መበታተን, ማለትም አልነበረም:: “ፍትሐዊ እድገት” ማለት ነበር!!
    “ኢትዮጵያዊያን በጋራ ሆነው አንድ ሀገራዊ ችግር የሚፍቱበት ጊዜ መቼ ነው?” ዛሬ ዙሪያውን የተሸጠ መሬት ለተወለደባት ኢትዮጵያዊ ዜጋ ሳይሆን ባለ ሀብቶቹ የራሳቸውን ቤተሰብ, ዘር, ጎሳ,እምነት እና ቋንቋ አምጥተው አጥር ከልለው በዚህ በኩል እንዳታልፉ ብለው ማስታወቂያ መለጠፍ ሲጀምሩ ወይም በይዞታ ቦታቸው አካባቢ ለመዘዋወርም ይሁን ለማለፍ ኪራይ ማስከፈል ወይም የይልፍ ወረቀት ኢንድናወጣ ማስገደድ ሲጀምሩ::ይሆናል ተጀምሯል ይቀጥላል!
    ከስሕተት መማር,ጥልቀት ያለው አመራርን ማዘጋጀት,የእያንዳንዱ እና የሁሉም ዜጋ ተሳትፎን ማካተት,እያንዳንዱ ዜጋ በራስ መተማመንን,ቁርጠኝነት,ተሳታፊነትን ማዳበር የሀገር ጉዳይ በግለሰቦች እጅ ሳይሆን በጋራ በሕዝብ ለሕዝብ እንደሆነ መረዳት,የሌሎችን ችግር ሐዘን ሰቆቃ እንደራስ አድርጎ እንዲሰማ ማድረግ,ከአሉባልታና ወሬ ከመጠራጠር የፀዱ መሆን,
    ሁልጊዜም ከተቀናቃኝ ጎራ ለሚሰነዝሩ ጥቃቶች ቦታ አለመስጠት,በተቃራኒው ግን ሕዝብ የተሻለ ግንዛቤ ኢንዲኖረው ማስተማር ማወያየት,ወቅታዊ ሁኔታዎችን ሁሉ ለሕዝብ እንዲደርሱ ሁሉም የመረጃ ምንጭ እንዲሆን ማሳተፍ,ልዩነቶችን ለማጥበብ ብሎም ጨርሶ ለማጥፋት መቀራረብ,ሂስ እና ግለ ሂስን ማቅረብ ማመን ወይ ማሳመን አለበለዚያ የጅምላ አንድነት የውስጥ ቁርሾ አጋጣሚን አድፍጦ መጠበቅ ፍጹም የችግር መፍትሔ ሳይሆን የችግር ወታቦ መሆን ነው በለው!
    ክቡር ዶ/ር አክሎግ ቢራራ ከምስጋና ጋር ከሀገረ ካናዳ በቸር ይግጠመን>>>>>>>>>>>>>>>>

  2. ዳኒ
    | #2

    ብዙ ኦድ አደር ቢኖርም እንደረሶ አይነቱ ታማኝ ደሞ ሞልቶልናል ወያኔ መወደቁ አይቀሬ ነው ሁሉም የት እንድሚገባ እናያለን ባለንበት አሾክሻኪወን እንዳይላወስ ማረግ እና ፍርዱን እንዲያገኝ ማረግ ነው ማንም እንዳይፈረጥጥ መጠበቅ አለብን ወያኔ አይወድቁ አወዳደቅ መውደቁ ቃይቀረምና. አቶ አክሎግ በጣም እንወዶታለን እናከብሮታለንም.

  3. እግዜር ይርዳን
    | #3

    በእኔ ዕይታ ከርስዎ ትንተናና መፍትሔ ጎደለ ያልኩትን ለማከል ያህል

    ትግሬን ሲዳማን (ከደቡብ ክልል) ጋምቤላ ሶማሊያ አማራ ኦሮሞ አፋር ክልልን በተመለከተ ተቃውሞው ለምን ጎላ ብሎ ከሌላው ክልሎች ይታያል? የመንግስትን ክልል አወቃቀርና በጀቱንና ፖለቲካ ትኩረትም ስንመለከት ጎላ ያለ ነው

    በቀሩት አካባቢዎች ያለው ችግር እንደጠስካቸው ክልሎች ትኩረትም ድምጽም አያገኝም
    ይህም የሚያንጸባርቀው የውጮቹ አገሮችን የረጅም ግብ ያሳያል ሪሶርስንም ይመለክታል
    ይህም የመንግስትም ሆነ የተቃዋሚ ትኩረት ጎላ አድርጎታል
    ስለዚህም በሕዝብ መካከል ያለ ችግር ሳይሆን የውጮቹ ገንዝብና ድርጅቶች ጥቅማቸውን ያስክብሩኛል ብለው ያመኑዋቸው አካባቢዎች ፓሊቲካ እንዲራገብ ድጎማ ያደርጋሉ
    ይህ ባይሆን ለመሆኑ ሶማሊያን ከጉራጌ ለምን የተለየ በደል ኑሮት ነው ርዳታው የሚጎርፍለት ሲዳማ ከወላይታው ምን ለይቶት ከፍተኛ ፓለቲካ ትኩረት የሚሰጠው ትግሬ ከኦሮሞ ለምን ለሥልጣን ተመረጠ

    መፍትሔው ሁላችንም የውጩን አንጋሽነት መረዳትና ይሄ ሃይል እንዴት አርጎ ቢያዝ ሚዛን እንዳደፋ ለማድረግ ስንነሳ ነው
    ማንም እንደሚያውቀው የየትኛውም ክልል ገበሬ መሬቱን የሚያርሰው ያው በጥንቱ ባህል ነው የሚኖርውም በሳር ጎጆ ነው
    ችግሩ አንዱ ጎሳ መሪ መሳሪያ ከውጭ አገር ለምኖ ወይም ተችሮለት ወገኑን የሚያስገብር ባህል አሁንም በውስጣችን እንዳለ መረዳትና አንዳችን ለሌላችን ክብር የምንሰጠው ይሐ ባህልና ብልጣብልጥነት እንዲቀር ስንታገል ነው

    ሃይማኖት አስታኮ ከሚደርስብን ችግር አንዱን እየረዱ ሌላኛውን ዝቅ ወይም ከፍ የሚያደርጉት ቡድኖች ናቸው
    ይህንንም ተግንዝበን መፍትሐው አብሮ መስራት እንጂ የውጭ ገንዘብ እየተቀብሉ ይሄ ሃይማኖት አገራችን እንዲህ አድረገ ብሎ መኮነንን ማቆም

    ዞሮ ዞሮ ድሃው ምስኪን በመካከሉ ብዙም የከረረ ችግር እንደሌለው ሁላችንም እናምናለን
    ይቺ የፈረንጅና የዓረቡን ገንዘብ መሳሪያ ፕሮፓጋንዳ እየተከተልን የምናስተጋባውን መፈተሽ ማረም ነው

    በተረፈ እግዜር ይርዳን

  4. በላይነሽ
    | #4

    የተከበሩ ዶ/ር አክሎክ ያቀረቡት መሰረታዊ ሃሳብና በውስጡ ያቀረቡት ትንተና ግሩም ነው::ሊደነቅ የገባዋል::ብዙ ሰው አንብቦ የራሱን ሃሳብ እንዲገልጽ በርም ይከፍታል::
    በዚህ ጹህፍ ያላየሁትን አንዳንድ ሃሳቦችና ጥያቂዎች ላንሳ::
    በኢትዮጵያ የዘረኝነትና የጎሳ ፖለቲካ መነሻው ምን እንደሆነ አልተዘረዝረም::የችግሮችን ምንጭ ለማድረቅ ምንጩ መታወቅ አለበት::የጎሳፖለቲካውና ዘረኝነቱ በህዝቡ መሃከል ለምን አልሰረጸም? ችግሩ ያለው በፖለቲከኞች አካባቢ ነው ይህ ለምን ሆነ?ዘረኝነትን ወያኔ አራገበውና ተገበረው እንጂ በዋናነት ምንጩም አይደለም::
    ዕድገት አለ የለም ብሎ መከራከሩ የሚፈይደው ነገር የለም::ዕድገት አለ ማለት ይቻላል::ዕድገቱ በሰላም ከአልተደገፈ በአንድ ቀን ለሊት ፈርሶ የሚያድር ነው::የእድገት መሰረቱና ምሰሶው ሰላም ነው::የድገት መሰረቱ ሞራል ነው::
    አሁን ያለው ዕድገት በተዳከመ ሞራልና ሰላም ላይ የተመሰረተ ለህዝብ ዋስታን የማይሰጥ ዕድገት በድቡሽት ላይ የተመሰረተ
    ያደርገዋል::ከዚህ እይታ መታየት እንጂ እድገቱ በያአመቱ7% እንኳን ቢሆን በቂ ነው::
    አማራው የሚደረስበት የስዕነልቦና ጫና የሚቃጣበ ከወያኔ በኩል ብቻ ነው የሚለው የተሳሳተ ነው::በዋናነት በተሽመደመዱ ፖለቲካን ሳያቁ ፖለቲከኛ መሆን የፈለጉ አማሮች ነው::የመጀመሪያ ይህን አራማጆች በኢህ.አ.ፓ ውስጥ የተሰገሰጉ ቆርፋዳ አማሮች ናቸው::2 ደረጃ ስግብግብና መንደርተኛ ፖለቲከኞች መ.አ.ሕ.ድ ውስጥ ተሰግስገው የነበሩ
    አቋም የሌላቸው ሰዎች ባሳዩት መከፋፈልና መበታተን ለአማራው የስዕነ ልቦና ውድቀት አቧራ ያስነሱ ናቸው::
    ቀደም ሲል በነበረው አንዲነትና መ.ኢ.አ.ድ የሚደረገው የስልጣን ሽኩቻ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል::
    በብ.አ.ሕ.ዴ.ን ብዙዎቹ በአቅም ማነስ የተጎዱና የተገላቱ ስለሆነ በዚህ ውስጥ አላካትታቸውም::
    ወያኔ አስተዋጾ ምን ይመስላል ለሚለው በትክክል ተገልጿል::ዓላማውም ስለሆነ ማድረግ ያለበትን ያደርጋል::መኮነን የለበትም አላልኩም::
    በውጭ ያሉት ፖለቲከኞች በአብዘሃኛው በውዕቀት እጥረት የተጎዱና የተጎሳቆሉ ከመሆናቸው የተነሳ የሚሰሩትን አያውቁም::የውቀት ድርቅ ከው አድርጓቸዋል::በቤታቸው ስንጥር መጽሃፍት የላቸውም::በጥራዝ ነጠቅ ነው የሚናገሩት::
    ይህም ሊነገራቸው ይገባል::የስም ማጥፋቱም ምንጩ የውቀት ድርቁ ነው::
    ለትብብር ችግር የፈጠረውም ይኽው መናጢ ችግራቸው ነው::ድሮ ተማሪ እያሉ የሚያነሷትን ሃስብ ነው አሁንም የሚያነሱት::ስፋ አድርገው ዕቅድ አውጥተው ለመንቀሳቀስ አቅም አጡ::
    ስልጠና ቢስጣቸው ይደገፋል::አንድ የኢትዮጵያ ፖለቲከኞችን የሚያሰለጥን አንድ አካል ቢመሰርተና ዶ/ር አክሎክ
    ቢያስቡበት መልካም ነው::እኔም ስልጠናውን የሚሰጡ ሰዎች ማመቻቸት እችላለሁ::

  5. ሰላማዊት
    | #5

    በላይነሽ የምትሰጣቸው አስተያየቶች በጎና መጥፎ ጎኖች ሲታዩ
    ብዙዎቹ የበላይነሽ አስተያየቶች ጉንተላ ይበዛባቸዋል::እነዚህ ጉንተላዎች የስውን ሞራል ያደቃቅቃሉ::የምትጠቀማቸው ቃላት ጠንካራ ስለሆኑ በመጥፎውም ሆነ በጥሩ መልኩ የማሽነፍ ሃይል አላቸው::
    እስካሁን የምታቀርባቸው ሃሳቦች በሌሎች ሰዎችም አንደበት ሲነገር ይሰማል::ጥንቃቂና መታስብ ያለበት በላይነሽ የፈለገችውን ሃስብ በራሷ አመለካከት የመሳብ አቅም ስላላት በጥንቃቄ መታየት አለበት::ከ2ኛ ደረጃ እስክ 5 ኪሎ ድረስ አውቃታለሁ::ይህ ማለት ግን በኢትዮጳዊነቷ የምትጠረጠር ልጅ አይደለችም::እልከኛሰለሆነች ጎሽምሽም ከአድረጓት በልክ ገደል ይዛችሁ እንዳትገባ አስቡ::

  6. በላይነሽ
    | #6

    ምነው ሰላማዊት?
    ኢትዮጵያዊ ወኔና ዕልክ ኢንጂ ሌላ መጥፎ አመል የለብኝ::
    ይህም ለስራ ተፎካካሪነት ይበጃል ኢንጂ መጥፎ አይደለም::
    ተንኮለኛም አይደለሁም ተተናኩየም አላውቅም::
    ለምን የሞኝ ዘፈን ትዘፍኒያለሽ?

  7. ሰው አየ በ.!
    | #7

    ሰላማዊት :
    በላይነሽ የምትሰጣቸው አስተያየቶች በጎና መጥፎ ጎኖች ሲታዩ
    ብዙዎቹ የበላይነሽ አስተያየቶች ጉንተላ ይበዛባቸዋል::እነዚህ ጉንተላዎች የስውን ሞራል ያደቃቅቃሉ::የምትጠቀማቸው ቃላት ጠንካራ ስለሆኑ በመጥፎውም ሆነ በጥሩ መልኩ የማሽነፍ ሃይል አላቸው::
    እስካሁን የምታቀርባቸው ሃሳቦች በሌሎች ሰዎችም አንደበት ሲነገር ይሰማል::ጥንቃቂና መታስብ ያለበት በላይነሽ የፈለገችውን ሃስብ በራሷ አመለካከት የመሳብ አቅም ስላላት በጥንቃቄ መታየት አለበት::ከ2ኛ ደረጃ እስክ 5 ኪሎ ድረስ አውቃታለሁ::ይህ ማለት ግን በኢትዮጳዊነቷ የምትጠረጠር ልጅ አይደለችም::እልከኛሰለሆነች ጎሽምሽም ከአድረጓት በልክ ገደል ይዛችሁ እንዳትገባ አስቡ::

    ሰላማዊት አሁንም ባለሽበት ሰላሙን ይስጥሽ !ለመሆኑ ዲያስፖራው ዝም ብሎ ቱልቱላውን ይነፋል? በላይነሽ እንደ ወጧ እንዳማረላት ገረድ እንዲሁ ሰው ሀሳብ ከመስጠቱ በፊት ተሽቀዳድማ ጸሐፊውንም ሀሳብ ሰጭውንም እንደ አበደ ውሻ ስትለክፍ ትታያለች። አዎን ብዙ የሚያውቋት የወጣላት ባለጌ፤ መደዴ፤ ሁሉን አዋቂ፣ሰው ናቂ፤ እንደሆነች ይመሰክራሉ። በጣም ሰው ትዳፈራለች…
    “በኢትዮጵያ የዘረኝነትና የጎሳ ፖለቲካ መነሻው ምን እንደሆነ አልተዘረዝረም::የችግሮችን ምንጭ ለማድረቅ ምንጩ መታወቅ አለበት:(ታዲያ አንቺ ዕውቀቱ ገንዘቡ አለኝ የምትይው ፈልገሽ ድረሽበት።)

    ” ዕድገት አለ የለም ብሎ መከራከሩ የሚፈይደው ነገር የለም::ዕድገት አለ ማለት ይቻላል። እድገቱ በያአመቱ7% እንኳን ቢሆን በቂ ነው::” (ታዲያ እድገት ካለ ትግል ለምን አስፈለገ?ያነቺስ መቀሳፈት፤ለስድብ እና ዝልፊያ ለምን መጣሽ?)
    አማራው የሚጠቃው በራሱ “በዋናነት በተሽመደመዱ ፖለቲካን ሳያቁ ፖለቲከኛ መሆን የፈለጉ አማሮች ነው:” እነማን ናቸው? ? ?”በኢህ.አ.ፓ ውስጥ የተሰገሰጉ ቆርፋዳ አማሮች ናቸው::2 ደረጃ ስግብግብና መንደርተኛ ፖለቲከኞች መ.አ.ሕ.ድ ውስጥ ተሰግስገው የነበሩ….”(በብ.አ.ሕ.ዴ.ን ብዙዎቹ በአቅም ማነስ የተጎዱና የተገላቱ ስለሆነ በዚህ ውስጥ አላካትታቸውም::ማለትም አብዛኛዎቹ ወያኔ አስፈንድዶ የሚጋልባቸው ቅጥረኛ በውጭው(ዲአስፖራው)ውስጥ ሰርገው እንደ በላይሽ ደርበው ተመስገን(ነብሮ)ቀበሮ የውሸታቸውን ተባበሩ እያሉ ለወያኔ በብ.አ.ዴ.ን ሥም ሚስጥር የሚቀብሉ እንደ ቤልጂግ አሊን የሚሳደቡ የሚያጥላሉ ቀበኞች ናቸው።
    “በውጭ ያሉት ፖለቲከኞች በአብዘሃኛው በውዕቀት እጥረት የተጎዱና የተጎሳቆሉ ከመሆናቸው የተነሳ የሚሰሩትን አያውቁም::የውቀት ድርቅ ከው አድርጓቸዋል::በቤታቸው ስንጥር መጽሃፍት የላቸውም::በጥራዝ ነጠቅ ነው የሚናገሩት::” (ወይ መቀሳፈት…ወይ በአፍ መፀፀዳዳት ..ባለጌ:መረን:ወፍጮ-ላሽ:ሌባ:ሆድ አደር ድሮሰ ወሎ..
    “አንድ የኢትዮጵያ ፖለቲከኞችን የሚያሰለጥን አንድ አካል ቢመሰርተና..እኔም ስልጠናውን የሚሰጡ ሰዎች ማመቻቸት እችላለሁ::” አሁን እውነትም አቡጊዳም ሆነ ምሁር ተብዬ ተቃዋሚዎች የመፈተሻቸው ጊዜ መጣ ?ጎበዝ ንቃ ነገር አለ ጠርጥር ሳትመነጠር !! ሰላማዊት በድጋሚ ስለማሰተዋል ችሎታሽ እንደቀደሞው ሁሉ አድናቆቴ ይድረስሽ በጣም ጎበዝ!!በርቺ…ኢትዮጵያ የጠፋባት የተማረ አስተማሪ ሳይሆን አድፍጦ እውነትን ከሐሰት የሚለይ ነው አስተያየት ቁጥር ሰባት ተማፅናችሁ ካላስጠፋችሁት።ልብ ካላችሁ ግጠሙኝ የማንም ፓርቲ፣ጎሳ፣ነገድ፣ብሔር፣አራማጅ ወይንም ጀሌ አደለሁም!!!የጠራሁ ኢትዮጵያዊ ነኝ !!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!

  8. ሰላማዊት
    | #8

    በላይነሽ ያንች እልህ ከመጠን በላይ ነው;;ይህ እልህናለምን ተነካሁ ለሰዎችም ለአንችም ጥሩ አይደለም:;
    አልፎ አልፎም ከመጎተል አልፈሽ መምታትም አለ::አጼበጉልበቱ ብትሆኝም ክፉ ገጥሞሽ አያውቅም::
    አሁንም በውቀት በልጽገሽና የቤተስብ ሃላፌ ሁነሽ ያው ባህሪሽ አለቀቀሽም::
    እኔም እንደገለጽኩት ክፉነች አልወጣኝም::የተጋነነ ደግነት ታታሪና ጎበዝ መሆንሽንም መስክሬያለሁ::
    ወደ ፈለግሽው የመጠምዘዝና የሃሳብ የበላይነት ለማገኝት ወደ ኋልም የማትይ መሆኑን አሁንም እገልጽልሻለሁ::
    በገሃድም እየታየ ነው::ደግ ደጉን ሃስብሽን እንዲወስዱ መናገር አበሳ የለውም::
    በእኔ አነጋገር መከፋት ይቅርብሽ::

  9. እግዜር ይርዳን
    | #9

    በላይነሽ ባላውቅሽም በአካል
    ሰላማዊትን ስሚያት
    እንዲህ ያለ ጋደኛ እህትም እናትም ያውም አድናቂሽም ናት
    ለምን ብትይ ታውቅሻለሽ ታከብርሻለሽ ደግሞ ታርምሻለሽ
    ባላውቃችሁም እንዲህ እህቶች ብኖሩኝ ኑሮ ነው ያልኩት ወንዶቹን ተያቸው
    ጠንካራ ሴቶች በብዛት ቢኖሩን ወልፋጣ ወንዶች አይኖሩም ነበር
    ሰላም ሁኑ

  10. ዳኒ
    | #10

    ሰው አየ በ. እወነት ለመናገር ማንነትህን ልንገረህ አንድ የቤት ሰራተኛ እንኳን ማን እንደሆንክ በጽህፍህ ታውቅሃለች. የተናገረካት ነገር ማንንትህን ታጋልጣለች. ዛሬ ነጭ ነገ ጥቁር ነኝ የምትል የወያኔ ቡችላ ነህ!!!!!!! አይክፋህ ወያኔ ብትሆን ሰው ነህ.ድርጅቶችን ጠቅሰህ እንዲህ ናቸው ብክለሃል ኮረንቲ መጨበጥ ትችላላህ ከወያኔ የማይሻል የለም ሌላወን ለመስደብ መጀመርያ ተሽሎ መገኘት ይጠበቅብሃል.ለመሃይም ጊዜ ማጥፋት አልፈልግም ይበቃል ሞት ለወያኔ እና ለውሾቹ!!!! አቶ አክሎግ ዪትዮፒያ አምላክ የጠብቆት ወያኔ ማለፉ አይቀረም ከማይልፈው ህዝብ ጋር መቆሞት ትልቅ እና ታላቅ ነገር ነው አከብሮታለው. በርቱ!!!!!!!!!!

አስተያየት መስጫው ተዘግቷል።