ግልፅ ደብዳቤ ለኢሳት (ESAT) ና ታዳሚዎች!!!አንተነህ ሽፈራው
‘የነገዋ ኢትዮጵያ በዛሬው ቅይት ትለካለች’:-
ወያኔ የየካቲት 1967 ዓ.ም አፈጣጠሩ፣ እድገቱ፣ አሁን እየሠራ ያለው ተግባሩ፣ ቀጣይ ዓላማውና እንዲሁም በ1997 ዓ.ም ምርጫ እርቃኑን የቀረው ዘረኛ የፖለቲካ መሠረቱና ኋላቀርነቱ ኢትዮጵያን መሠረት አድርገው ከተደራጁ ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ቡድኖችና ከግለሰቦች ጋር ሳይቀር ለሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ ስልጡን የፖለቲካ ሥርዓት ተገዥ ሆኖ ለሥልጣን ለመወዳደር ስለማይፈቅድለት ሕዝባችንን አረመኔ በሆነ ድርጊቱ በጠብ-መንጃ በገፍ ይገላል፣ የአገር ንብረት ይዘርፋል፤ አልፎ አልፎ ብቅ ብቅ ያሉ ጠንካራ ጋዜጠኞችም ከመጠን በላይ ስለሚያስፈሩት ያለአግባብ ለተደጋጋሚ ግዜ በእስር ፍዳቸውን አሳይቶአቸዋል፤ የሚወዷት አገራቸውን፣ ሕዝባቸውንና ቤት ንብረታቸውን ትተው ለስደት ዳርጓቸዋል፤ አሁንም ድረስ እልፍ አህላፍ የሕሊና እስረኞችና ጋዜጠኞች ቀድሞ በነበሩትና ወያኔ በከፈታቸው ተጨማሪ እስር ቤቶች በገፍ እየተንገላቱ ይገኛሉ::
ደፋርና ጭስ መውጫ አያጣም እንደሚባለው ሁሉ ‘ኢሳት/ESAT ይህን ሁሉ የወያኔን የአፈናና ግድያ ሰብሮ ሰባብሮ የወጣ ከነፃ ሚዲያነት ወደፊት ወደ ኢትዮጵያዊ ሁለንተናዊ (የዜናና መረጃ) ማዕከልነት ጭምር ሊያድግ ሊመነደግ እንደሚችል ብሩህ ተስፋ ያለው መሆኑ ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያውያን ሁሉ ‘ያይበገሬ ምልክትም ሆኖ’ ሊጠቀስ የሚችል ይመስለኛል:: ለዚህም ዋናው ምልክት ደግሞ ኢሳት ከግለሰቦች ጅማሮ ወሳጅነት ወጦ በቅርቡ ኢሳትን ለማጠናከር ተብሎ በተዘረጋው መርሃ-ግብር ላይ ኢትዮጵያውያን እያሳዩ ያሉት ተሳትፎና ጥረት አበረታች ሆኖ መገኘቱን ይጠቅሳሉ – - – በግል አስተያየቴ:: እርግጥ ነው ለኢሳት/ESAT መነሻ እንደ ጥሩ ተምሳሌት/አርያ ሆነው ያገለገሉ የመረጃ ተቋማትን ለአፍታም ቢሆን መርሳት የለብንም:: በዚህ ረገድ አበበ በለው ለረጅም ግዜ እያደረገ ያለው የሬድዮ ሙከራና ኢቶ-ሚዲያ፣ ቋጠሮ፣ በተለይ ደግሞ አሁን አሁን እጅግ በጣም ተወዳጅ እየሆነ የመጣው አቡጊዳና ሌሎችም ድህረ-ገፆች ያለምንም በቂ የፋይናንስ አጋዥ ሙሉ ግዜያቸውን በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ቤዛ በማድረግ ኢትዮጵያውያን እርስ በእርስ ሓሳብ እንድንለዋወጥና እንድንማማር ጠንካራ ድርድይ ሆነው እያገለገሉ መሆናቸው ለአፍታም እንኳ ቢሆን የሚዘነጋ አይደለም – - – ምንም እንኳን አንዳንድ ግዜ ጽሑፎቻችን በዚያው ቀልጥው የሚቀሩበት ሁኔታ ያሉ ቢሆንም ቅሉ::
ኢትዮጵያ አገራችን በባይታወር የፖለቲካ ሽኩቻ አደጋ ላይ ወድቃ አምባገነኑ ደርግ/መኢሶንና ኢሕአፓ እርስ በእርስ በመሓል አገር ‘አገር ተረካቢውን ጠንካራ ትውልድ እንደቅጠል ሲቀጥፉት’ ወያኔዎች የተፈጠረውን መልካም አጋጣሚ በመጠቀም እራሳቸውን አደራጅተውና በታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላት አገሮች ታግዘው የበለጠ ኃይላቸውን ሲያጠናክሩ በሌላው በኩል ግን ‘በእንቅርት ላይ ጀሮ ደግፍ’ ይሉ በትጥቅ ትግሉ ውስጥ የነበረው ኢሕአፓ የራሱን የውስጥ ችግር መፍታት አልችል ብሎ በ1973 ዓ.ም ከፍተኛ የሆነ የብተና ድርጊት ሲፈጠምና በሂደት አንጀኝ የሚባሉት የኢሕአፓን አመራራ አካላት ጎዳን ብለውና የጎሣ ፖለቲካ ሰለባም ጭምር ሆነው ራሳቸውን ለወያኔ ለሎሌነት (ኢህዴን በሚል ሽፋን ስጭ ስያሜ) አሳልፈው መስጠታቸው የኢትዮጵያን የፖለቲካ ችግር እጅጉን አደገኛ አደረገው::
ወያኔ በመንገድ መሪዎች በነታምራት ላይኔና ከኤርትራ በምርኮኝነት የተረከባቸውን እነ ኩማን (ታዬን) ይዞ መላ አገሪቷን ከመውረሩ በፊት ኢሕአፓ አካባቢ የነበረውን የትጥቅ ትግል ክፍተትና ቸልተኝነት ለመለወጥ ይረዳን ዘንድ ሰራዊቱን (ኢሕአሠን) በሞራልና በተለያዩ ስልቶች ለማጠናከር ሱዳን ካርቱም ላይ በወቅቱ የኢሕአፓ ጽ/ቤት ኃላፊዎች/አመራር የነበረውን አካል ደግመን ደጋግመን ሜዳ ሄደን ሰራዊቱን እንድንቀላቀል መስመር እንዲሰጠን ብንጠይቅም “የኢሕአፓን ሰራዊት ለመቀላቀል መጀመሪያ የኢሕአፓ (የፓሪቲ) አባል መሆንን ይጠይቃል” በሚል ቢሮክራሲ ጥረታችን ሁሉ ከንቱ ሆኖ ቀረ:: ምንም እንኳን በወቅቱ ከ30 የማንበልጥ ሰዎች ሜዳ ገብተን የወያኔን የወረራ ድርጊት መለወጥ እንኳ ባንችልም ቅሉ በወቅቱ ኢሕአፖ የነበረውን የትጥቅ ትግል እርሾና ጥሪት ከወያኔ ዘርፋ አድነን በአዲስ ሞራልና የሽምቅ ውጊያ ስልት ወያኔን በሚገባው ቋንቋ ወዲያው ፈጥኖ ማነጋገር በተቻለ ነበር:: ይህ ባለመሆኑ ግን ወያኔ ጭራሽ የልብ ልብ ተሰምቶት በሰኔው 1983 ዓ.ም የሽግግር መንግሥት ተብዮው ላይ ኢትዮጵያውያን ድርጅቶች ሙሉ በሙሉ ተገለው በወያኔና የጎሣ ፖለቲካ ሰለባ ባደረጋቸው ሽፋን ስጭነት (ኦነግን ጭምሮ) የኢትዮጵያ ሕዝብ ታሪካዊ አሰፋፈርና ካርታ በእብሪት ተሸንሽኖ በአገር ላይ አገር ተፈጥሮ በነባር የከተማ ስሞች ላይ አዲስ ስምች እየወጡ ወያኔ በብቸኝነት በሚቆጣጠረው የሕዝብ የብዙሃን መገናኛ ሚዲያ ተቋማት ለሕዝብ ቀረቡ:: እነዚህ አዳዲስ አከላሎችና ስያሜዎች ወያኔ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከሚጠቀምበት የወታደራዊ ኃይሉ ቅጥዮች መሆናቸውን በሚገባ መገንዘብ አለብን::
የዚህ ጽሑፍ ዐብይ ዓላማም የወያኔን ማሳደድና አፈና ሰብሮ ሰባብሮ ለመውጣት ከፍተኝ ጥረት እያደረገ ያለውንና የሁላችንንም እገዛ የሚሻውን ኢሳት/ESAT ለመወንጀልና ለማሳጣት ሳይሆን ኢሳትና ታዳሚዎቿ በነዚህ ወያኔ ከፋፎሎ ለመግዛት እንዲያመቸው ብሎ በከለላቸው የከፋፍለህ ግዛ ክልሎችና አዳዲስ የከተማ ስያሜዎች ላይና ከዚሁ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ ግልፅ ግንዛቤና አቋም እንዲኖረው በማድረግ ኢሳት/ESAT ዛሬ በተለያዩ ክልሎች ተከፋፍላ በወያኔ መዳፍ ውስጥ ገብታ የምትመዘበረው ኢትዮጵያ ነገ ሁሉም ዜጎች በዴሞክራሲያዊና ሰላማዊ መንገድ ተቻችለውና ተጋግዘው፣ ቋንቋቸውና ባሃላቸው ተከብሮ በእኩልነት የሚኖሩባት ኢትዮጵያን ለመፍጠር ከተፈለገ ኢሳት/ESAT የወያኔን አዲስ አከላለል፣ የከተሞችና የተቋማት አሰያየሞች ከሚዲያ ማዕከሉ ሙሉ በሙሉ ነቅሎ ማውጣት አለበት:: ጉዳዩን የበለጠ ግልፅ ለማድረግ ያህል ዘንድ በአንድ ኢትዮጵያ ውስጥ ኦሮሚያ፣ አማራ፣ ወዘተ የሚባል አገር የለም:: በሌላ አነጋገር ኦሮሚያ፣ አማራ፣ ወዘተ የሚባል አገር በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ታይቶም ተሰምቶም አይታወቅም/አልነበረም ወደፊትም አይኖርም:: የሚኖረው አንድና አንድ አገር ብቻ ነው:: ያም ኢትዮጵያ የሁሉም የበላይ የጋራ አገር ሆና ለስልጣን ክፍፍሉና ለአስተዳደር እንዲያመች ግን ከጥንት ጀምረው የነበሩ የክፍለ ሀገር ሥሞች ከጎሣ ስያሜነት ነፃ የሆኑ በመሆናቸው ወደፊትም ያገለግላሉ – - – ዜጎችም ክፍለ-ሀገር ሳያግዳቸውና ጎሠኝነት ጫና ሳይፈጥርባቸው በሚፈልጉት ቦታ (ክ/ሀገር) ተንቀሳቅሰው የመኖርና ሃብት የማፍራት ሙሉ መታቸው ሊሸራረፍ አይገባምና::
እርግጥ ነው ኢጣሊያን አገራችንን በወረረ ግዜ የኢትዮጵያን ሕዝብ በጎሣና በሃይማኖት ከፋፍሎ ለመግዛት ይመቸው ዘንድ ቀድሞ የነበሩ ክ/ሀገሮችን በጎሣ አካሎ አማራ፣ ኦሮሞ-ሲዳሞ፣ ሱማሌ፣ እስላምና ክርስቲያን በማለት ይጠቀም የነበረ መሆኑ በሚገባ ቢታወቅም የኋላ-ኋላ ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ የኢጣሊያን የመከፋፈል አሽክላ ሰብሮ የመጣውን የውጭ ጠላት አብሮና ተባብሮ አሳፋሪ በሆነ መንገድ ወደ መጣበት መልሶታል:: ዛሬ በወያኔ እስር ቤት በግፍ እየተንገላታ ያለው አበበ ደብተራው “የሞሶሎኒ ጦር” ብሎ የሚጠራው ወያኔ ግን ያ የበፊት አለቆቹ የወጠኑትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ ሲል የጎሣና የሃይማኖት ክፍፍሉን በአዲስ መልክ ጭራሽ አባብሶ መልሶ ስላመጣው ኢሳትና ታዳሚዎች ግልፅ አቋም ይዘው ሊመክቱት ይገባል እንጅ ወያኔና እነ ስዬ አብርሃ፣ ገብሩ አሥራትና ነጋሶ ጊዳዳ እንደዚሁም ቢጤዎቻቸው እርቃኑን የቀረውን ወያኔን ኢህአዴግ፣ ናዝሬትን አዳማ፣ ወልቃይት-ጠገዴንና ሴቲቱ-ሁመራን ትግራይ ክልል፣ አዲስ አበባን ፍንፍኔ፣ የተለያዩ ክ/ሀገሮችንና ቋንቋውን እንኳ መስማትና መናገር የማችሉትን እጅግ በጣም ብዙ የሕብረተሰብ ክፍሎችን አንድ ላይ ጨፍልቆ ኦሮሚያና አማራ ወዘተ እያሉ የሚጠሩትን ተቀብለን የምናስተጋባበትና ታሪክ የምናዛባበት ሁኔት ጭራሽ መኖር የለበትም:: ኢሳቶች ወያኔን ኢህአዴግ- ናዝረትን አዳማ – የተለያዩ ክ/ሀገሮችንና ማኅበረሰቦችን አንድ ላይ ጨፍልቀው ኦሮሚያ፣ አማራ፣ . . . ወዘተ የሚሉ ስያሜዎችን በምሰማ ግዜ የወያኔ የዜና ማዕከል አልያም የእነ ስዬ አብርሃና ገብሩ አሥራትን አንደበት የማዳምጥ ይመስለኛል::
በተለይ ደግሞ ይህን ጽሑፍ ግልፅ ደብዳቤ ለኢሳት በሚል እንዳቀርብ ያስገደደኝ ዐብይ ምክንያት የኢሳት ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም ከአባ ኒቆዲሞስ ጋር ያደረገውን ቃለ መጠይቅ በጽሞና በተከታተልኩ ግዜ በአንድ ቃለ-መጠይቅ ውስጥ የተለያዩ ገፀ-ባሕሪዎችን አዳብሎ ያያዘ መሆኑን መገንዘብ በመቻሌ ነው:: በመጀመሪያ ነገር ኢሳት ይህን የወያኔን፣ የኦነግን፣ የኦህዴድንና የነታምራት ላይኔን የአማራንና ኢትዮጵያን የሚወዱ የሕብረተሰብ ክፍሎች ዘር እየተፈራረቁና በጋር ርብርብ በማጥፋት ተግባር ላይ እንደተሰማሩ በሚገባ የሚይሳይ ምስክርነት አፈላልጎ ማቅረቡ የሚያስመሰግነው ቢሆንም ቅሉ ፋሲል የኔዓልም ግን የተከበሩ አባ ኒቆዲሞስ ኦነግ የሰራውን ዘር በማጥፋት ድርጊት ለዘብ አድርገው ወደ ወያኔ ብቻ እንዲያተኩሩ ለማድረግ ያደረገው እጅግ በጣም ከፍተኛ ጥረት ልክ አንድ ፍርድ ቤት የቀረበ መስካሪ ይህን ብለህ መስክር የሚባል ዓይነት ሕገ-ወጥ አቀራረብ ከማድረጉ በተጨማሪ “ምናልባት ነግ ኦነግ በተመሳሳይ ሁኔታ ኦሮሚያን ቢያስተዳድር ሌላ ቋንቋ ተናጋሪ በሆኑ የሕብረተሰብ ክፍሎች ላይ ችግር አያመጣም” ወደ ሚል መደምደሚያ እንዲሄዱለት ለማድረግ መሞከሩ ለመሆኑ ከወያኔ መውደቅ በኋላ ኢሳት በራሱ መነፀር የሚመለከታት ኢትዮጵያ ያለ ታሪካዊ መሰረትና አግባብ ወያኔና ኦነግ ኦሮሚያ ብለው የፈጠሩትን አዲስ አገር ለኦነግ አሳልፎ የመስጠት ዕራይም ይኖር ይሆን? የሚል እይታ አህምሮዬ ላይ ተሰክቶ በመቅረቱ ከወዲሁ እንደዚህ ካለው አካሄድ ኢሳት ራሱን አጥድቶ ወደ ትክክለኛው አቅጣጫ እንዲመጣ ለማመላከት ነው::
እዚህ ላይ አንድ ግልፅ መሆን ያለበት ጉዳይ ወያኔ ከመጀመሪያውም ጀምሮ ትግል ሲጀምርና (ከዚያም በፊት ቢሆን) የአማራን ዘርና ኢትዮጵያን የሚወደውን የሕብረተሰብ ክፍል ጭምር አብሮ ደርቦ አስቀድሞ በማጥፋት ኢትዮጵያን በማዳከምና በሂደትም በመበታተን ታላቋን ትግራይ ለመመስረት የተመሠረተ ዘረኛና ኋላ-ቀር ድርጅት መሆኑ በሚገባ የሚታወቅ ሆኖ ሳለ የኦነግን ተመሳሳይ ዘር የማጥፋት ድርጊት ለመሸፋፈን መሞከር ግን ‘ወያኔን በኦነግ የትግራይ ተስፋፊነትን በታሪክ ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ አዲስ ኦሮሚያ አገር’ የመተካት ያህል ከመሆኑ ባሻገር ደማቸው ባለድረቀ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ላይም መሳለቅ ይሆናል:: ለዚህም ነው ኢሳት ነገ ሊያያት የሚፍልጋት ኢትዮጵያ በዛሬው የኢሳት ቅይት ውስጥ ትታያለች በሚል ርዕስ የተነሳሁ::
በዚሁ ቃለመጠይቅ የፋሲል የኔዓልም አቀራረብ ኦነግን በመሸፋፈን ላይ እጅግ በጣም እርቆ የሄደ በመሆኑ የቀድሞው የኦነግ መሪ የነበሩት ዶ/ር ዲማ ነጎ እንኳን በአንድ ወቅት በጉዳዩ ላይ በኢሳት ቴሌቭዥን ቀርበው “በአማራ ሕዝብ ላይ ደረሰ የሚባለው ጥቃት በነፃ አጣሪ አካል ይጣራ ብለን በይፋ ብንጠይቅም ወያኔ ፈቃደኛ አልነበረም” የሚለውን አቋማቸውን እንኳ የሚጋፋ በመሆኑ እጅግ በጣም አዘንኩ:: እርግጥ ነው የፋሲል አካሄድ ምንግዜም ቢሆን ዋናው የአገርና የሕዝብ ጠላት ወያኔ በመሆኑ ሁሉም ኃይል በወያኔ ላይ መረባረብ ቅድሚያ ሊሰጠው ይገባል ከሚል አግባብ ተነስቶ ሊሆን እንደሚችል በሚገባ ብገነዘብም ቅሉ በሕዝባችንና በጋራ አገራችን ላይ ደባና ወንጀል የፈፀሙ ሁሉ ያለምንም ሽፍንፍን በሕግ ፊት መቅረብ ይኖርባቸዋል::
ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ “አዲስ አበባ ላይ የፈሰሰ ደም አለ” እያለ ተከታዮቹን ብዙ ብዙ ይሰብክ ነበር:: ለመሆኑ ማን የማንን ደም አፈሰሰና ነው ያልሆነ ታሪክ ለተከታዮቻቸው የሚሰብኩ? ዶ/ር ነጋሶ ሐረር ጨለንቆ ላይም በንጉሰ ነግሥቱ ዐፄ ዮሐንስ ትዕዛዝ መሰረት ዐፄ ምኒሊክ በግብፆች ተሹሞ ከነበረው ከአሚር አብዱላሂ ጋር የተደረገውንም የታኅሣሥ 29 ቀን 1879 ዓ.ም ኢትዮጵያን ከግብፆች የተቀነባበረ ጦርነት መከላከልንም የኦሮሞን ሕዝብ እንደመውረር ተቆጥሮ ብዙ ብዙ ቀስቅሰውበታል፤ ንፁሃንን ዜጎቻችን አስገድለውበታል:: እውነቱ ግን ዐፄ ምኒሊክ ጦርነት ውስጥ ከመግባታቸው በፊት ለዕርቅ አስበው “ግባ እኔ ላንት ነው እንጂ የመጣሁት አገር ለማጥፋት አልመጣሁም:: ተገባህ ተተገዛህ አገር አልነሣህም ኋላ ይጠጥትሃል” (ተ.ጻ.መ በ1982 ዓ.ም ገጽ 291-2) ብለው መላዕክተኛ ወደ አሚር አብዱላሂ ላኩ:: አሚር አብዱላሂ ግን ዐፄ ምኒሊክና ሠራዊታቻው የፈሩ መስሎት መላዕክተኞችን አስሮ በማስቀረት ከግብፅ ያገኘውን መጠነ ሰፊ ትጥቅና ሰራዊት አሰልፎ አድፍጦ በዓለ ገና (ልደት) ቀን ምኒልክና ሠራዊታቸው በበዓለ ገና ቀን ጦርነት ውስጥ አይገቡም ብሎ ጅሃድ አውጆና ተዘጋጅቶ ለጦርነት ከሩቅ ሲመጣ ዐፄ ምኒሊክ በጦር መነጥራቸውን ከዙፋናቸው ፊት አቁመው በአጋጣሚ ስለተመለከቱት ሠራዊታቸው ያልተጠበቀውን ጥቃት በስልት ገብቶ እንዲገጥመው ወዲያው ትዕዛዝ ሰጡና ከከፍተኛ ጦርነት በኋላ የአሚር አብዱላሂ መድፎችና ወታደራዊ ትጥቆች ሊማረኩ በመቻላቸው የዐፄ ምኒሊክ ሠራዊት የኢሚር አብዱላሂን ጦር ድል ነሳው:: ነጋሶ ጊዳዳ ግን ይህን ጦርነት የኦሮሞን ሕዝብ እንደመጨፍጨ አድርጎ በመስበክ በደቡብና ሐረር አካባቢ በነበሩ የአማራ ተወላጆች ላይ እጅግ በጣም ከፍተኛ ወንጅል እንዲፈጠም ለወያኔ ተባባሪ ሆነ:: ለመሆኑ የሐረር ግንብ ተብሎ ዛሬም ድረስ የሚታወቀው መቸና ለምን እንደተገነባ ኦነጎችና ነጋሶ ትክክለኛ ታሪኩን ያውቁት ይሆን?
“Although Nur was unable to dislodge the Galla from the parts of the Chercher-Harar plateau which they had overrun and settled, his tireless campaigning and the wall which, according to tradition, he had built around the town, temporarily curbed the advance of the Baraytuma and saved Harar.” [Abir, p. 137, 1980].
“. . . the Baraytuma swept the area and destroyed many hamlets and villages as fas as the hirterland of Zayla. The town of Harar itself was besieged for a time and had it not been for the timely arrival of reinforcements from the coast it might also have fallen to the Galla. . . .” [Abir, p. 139, 1980].
“. . . Harar, however, gradually declined because its economy was adversely affected by the occupation of most of its lands by the Galla . . . “the fortunes of Zayla were always closely connected to those of Harar. It was, therefore, badly affected by Harar‟s decline and the deterioration of law and order in the whole region”” [Abir, p. 140, 1980].
“By 1570, exploiting the topography of Amhara and the character of its government and population, the Baraytuma began to raid westwards into Ethiopia‟s heartlands, as far as Gojjam and Dembiya. In the 1570s and 1580s, using Angot and Amhara (where the Wollo group began to settle) as their main bases they (mainly the Karayu-Azebu) pillaged Tigre, Begemder, northern Showa and parts of Gojjam. The Borana renewed their westward advance immediately after the departure of Serse Dingil in 1572. No longer hampered by the network of Chewa and the presence of royal army, they submerged the southern provinces and by 1576/7 penetrated Showa. In the coming years the numerous clans of the Mecha group moved west of Showa and began to raid Damot and nearby territories. Concurrently, their Tulama brothers began to settle in western and norhwestern Showa and to raid Gojjam across the Abbay. During the 1580s, while the Abitchu penetrated southern Showa, the Mecha and related groups occupied Bizamo and overran a large part of Damot. From there or from Showa their Sadetcha clans continued to expand towards the Omo-Gibe basin while, at the same time, their Afra-Gudru clans reached the Abbay from the south and increased their pressure northwards on Gojjam and westward on Damot”. [Abir, p.164, 1980].
ወያኔና እነ ነጋሶ ጊዳዳ በሕገወጥ መንገድ ለሸነሸኑት ክልል ከፍተኛ እውቅና በመስጠት ኦሮሚያ አዲስ አበባ ላይ ያላት መብት (legislation that would materialize the Oromia Regional State’s right over the capital Addis Ababa) በሕግ ተሎ ካልወጣልን እያለ አጥብቆ እየጠየቀ እንደሆን ለሕዝብ ለንባብ የቀረቡ እነ ካፒታል ዝርዝሩን አቅርበውት ነበር::
ወያኔስ እኛን እርስ በእርስ ካላጋጨንና ካላጋደለን የሥልጣን መሰረት እንደሌለው እየታወቀ ከቶ ለመሆኑ እነ ነጋሶ ጊዳዳና ኦነጎች ለምን ያልሆነ ታሪክ በመፍጠር በኢትዮጵያዊነቱ ኮርቶ የሚኖረውንና ለዛሬዋ ኢትዮጵያ እልውና ከሌሎች ወንዶሞቹ ጋር በመሆንና በመሰለፍ ከፍተኛ አስተዋህፆ ያደረገውን ኦሮምኛ ተናጋውን ወገናችንን ከአማራው ሕብረተሰብ ጋር በማጋጨት የማደርቅ ደም ማፍሰስ እንደፈለጉ አይገባኝም?
ከሁለት ዓመታት በፊት ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በኦሮሞ ወጣቶች ስብሰባ ላይ እንዲገኝ በተደረገ ግዜ የገዳ ሥርዓትን እንደ አንድ የአፍሪካ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግኝት አድርጎ በማቅረቡ እጅግ በጣም መደንገጥ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ፖለቲከኛ ነን የሚሉት ከራሳቸው አገር (ከኢትዮጵያ) ታርክ ጋር ጭራሽ የማይተዋወቁ መሆናቸው ይችን አገር የቱን ያህል እንደጎዳት ይጠልጥ ተገነዘብኩ:: ዶ/ር ብርሃኑ የገዳን ሥርዓት አፍሪካዊ በቀል የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ነው ብሎ የምስክርነት ቃሉን የሰጠበትን ምክንያት እውነትነት የሌለው መሆኑን የራሴን የግል ግንዛቤ ለማስጨበጥ አስቤ እጅግ በጣም ሰፊ ጽሁፍ የዶ/ር ብርሃኑ ሰነድ ለሕዝብ ለንባብ በቀረበበት ድህረ-ገጽ በኩል ብልክም ጽሑፌ እቀባ ተደርጎበት ሊወጣ አልቻለም:: ለነገሩ ዶ/ር ብርሃኑ በማያውቀው ታሪክ ውስጥ ገብቶ የምስክርነት ቃሉን ለመስጠት የሄደበት አካሄድ አሳዝኖኝ በወቅቱ ግዜዬን ላጠፋ ተገደድሁ እንጅ በዛሬ ላይ ቆመን (አገራችንና ሕዝባችን በታሪክ ታይቶ ተሰምቶ በማይታወቅ የወያኔ አደጋ ላይ ሁነው) ስለ ገዳ ሥርዓት የምንነጋገርበት ወቅት አልነበረም:: እናም በወቅቱ እንዲወጣ የላክሁት ጽሑፍ ለንባብ ባይበቅም የቀረብኝ ነገር የለም::
“As Amartya Sen said there is “nothing exclusively “Western” about valuing liberty or defending public reasoning . . . there is, in fact, a long tradition of participatory governance in Africa as well ” This certainly is not a debatable point for the Oromo community as the Gaada is the perfect example of this tradition in our own region.” [Identify politics and the struggle for liberty and democracy in Ethiopia, posted on Ethiomedia.com on Aug 2010. Dr Birhanu Nega, page 19].
ቢያንስ ቢያንስ የገዳ ሥርዓት ባሉት ስድስት የዕድገት እርከኖች ውስጥ ከመጀመሪያው ወደ ሚቀጥልው የሥልጣን ደርጃ ለመሽጋገር በስምንት ዓመታት አዳዲስ አካባቢዎችን በመውረርና ኗሪውን ሕዝብ በመግደል አልያም ቤት ንብረቱን ዘርፎ በማባረር በራስ ቁጥጥር ውስጥ እያስገቡ ወደፊት የመገስገስ ሥርዓት መሆኑን አለማወቅ ግን እጅግ በጣም የሚያሳዝን ከመሆኑ በተጨማሪ የገዳ ሥርዓት ነበር በሚባልበት ዘምን ላይ ኦሮሞ የሚባል ማኅበረሰብ ሳይሆን የነበረው የተለያዩ ቋንቋ ተናጋሪና የጎሣ (example: Baraytuma Galla, the Ittu, Humbana and Karayu tribes, they were many different tribes) ዝርያዎችና እምነት ተከታዮች የነበሩ መሆናቸውን አለማወቁ ጭምር ነው::
አንድ ግለሰብ የገዳ ስድስተኛው እርከን ላይ ሲደረስ ግን በአንድ ወቅት አፍለኛ ወራሪ፣ ጦረኛና የጦር የጎበዝ አለቃ (አባ ዱላ የሚባለው) እድሜው ስለሚገፋ በኋላ ደጀንነት ከነባሩ ሕዝብ የተዘረፉና ወደፊት በአፍለኛ ጦረኞች የሚዘረፍ ንብረትን፣ ከብቶችንና እፃናት ልጆችን እንዲጠብቅ ይደረጋል:: ይህን መሰሉን ሥርዓት ለኢትዮጵያ ሕዝብ መመኘት ግዜው ያለፈበትና ኢትዮጵያን ሕጅጉን ወደ ኋላ ያስቀረ ብቻም ሳይሆን ቀጣዩ ኑሮአችን አንዱ ሌላውን እንዲያሳድደው ከማበረታታት ያነሰ አይሆንም፤ አልያም የግዜአዊ የፖለቲካ ጥቅም ለማግኘት ተብሎ የሚደረግ አካሄድ ለሁላችንም የማይበጅ መሆኑን አለመገንዘብ ይሆናል:: . . . as Gada was set to achieve only a specific objective, i.e., to kill and raid on others society’s areas it was not convenient to model centralized administration structure that enables to govern by bringing these different clans at a specific given space in which this don’t allow it to have what Birhanu claimed it participatory governance!!
ዶ/ር ብርሃኑ በቅንጅት ግዜ በስለት አንደበቱ ያደረገው እጅግ በጣም ከፍተኛ እንቅስቃሴ ወያኔን እርቃኑን ያስቀረ ብቻ ሳይሆን አሁንም ዘረኛውን ወያኔ በሚያምንበት የትግል መንገድ አንለቀውም ማለቱን አደንቃለሁ – - – የትግሉ ጅማሮና አቅጣጫ ምን እንድሆን ማወቅ ባልችልም ቅሉ:: ሆኖም ግን አሁንም ቢሆን የዴሞክራሲያዊ አንድነት ኃይሉ ይበልጥ መተማመን ያለበት ‘ጥርት ባለ ኢትዮጵያዊ መሰረቱ፣ የእምነት ጽናቱና ታግሎ ሊያታግል በሚችል ተጨባጭ ተግባሩ’ መሆኑ በሚገባ መታወቅ አለበት:: በአንድ አጋጣሚ አንድ የቅርብ የትግል ባልደረባዬ የነበር ኢትዮጵያዊ አንጋፋ የኢሕአፓ ሰው የነበረው አቶ ሣሙኤል ዓለማየሁ ከዚህ ዓለም በሞት በመለየቱ ምክንያት በአሜሪካ በተደረገው የቀብር ሥነስርዓት ላይ ተገኝቶ ስለ ሟቹ የሚያውቀውን ሲናገር የሚከተለውን ብሎ ነበር:: “. . . አቶ ሣሙኤል ጥሩ ጓደኛችን የነበር መሆኑ ብቻ ሳይሆን ጥሩ ምሁርም ነበር፤ እኔ ምሁር የምለው በከፍተኛ የትምህርት ተቋም ውስጥ ገብቶ መማርን ሳይሆን ኢትዮጵያዊ ፍቅሩና መከራና የተለያዩ ፈተናዎች የማይለውጡት ጽኑ እምነት ያለውን ዜጋ ነው . . .” ብሎ መናገሩ ዛሬም ድረስ ትዝ ይለኛል:: ይሁን እንጅ አሁን አሁን ምሁር የሚባለው ግን ይህን መሰሉ ጠንካራ ትውልድ ሳይሆን የአገሩን ታሪክ እንኳን በአግባቡ የማያውቅ ግን ደግሞ በዘመናዊ የትምህርት ተቋማት ውስጥ ገብቶ ተማርኩ፣ ዶክተርና ፕሮፌሰር ሆንኩ የሚለውን (ብቻ) መሆኑ እጅግ በጣም ያሳዝናል:: ለመሆኑ ስንቱ ምሁር ነው ወያኔ በአ/አበባ ዩንቭርስቲ ውስጥ ለረጅም ግዜ ያገለግሉ የነበሩ አንጋፋ ፕሮፌሰሮች ተባረው የነሱን ቦታ በአዲስ ተመልማዮች እንዲሸፈን ሲደረግ የወያኔን አገርና ትውልድ የማምከንን ድርጊት በመቃወም በዩንቭርስቲው ውስጥ አላስተምርም ያለ? አልያም ራሱን ለወያኔ ምልምልነት አሳልፎ ላለመስጠት የወሰነ? These are key moral and ethical issues in which Ethiopia and Ethiopians Needed Most!!
እርግጥ ነው ከወያኔና ቢጤዎቹ ጋር የሚደረገው አገርና ሕዝብን የመታደግ ትግል ጽኑ ኢትዮጵያዊ ፍቅሩ፣ መከራና የተለያዩ ፈተናዎች የማይለውጡት እምነት ያለው ዜጋ መሆንን የግድ ይላል እንበል እንጅ በዘመናዊ የትምህርት ተቋማት ገብተው እውቀት የገበዩ ዜጎች ቀጥተኛ ተሳትፎና አመራር ሳይኖርበት የአገርና የሕዝብ እድገት ሊኖር እንደማችል ደግሞ በትግራይ ካድሬዎች የተሞላው የወያኔው መንግሥት ዐብይ ምስክር ነው::
ለዚህም ነው ኢሳት/ESAT ከግለሰቦች ጅማሮ ወሳጅነት አልፎ የወያኔን አሰልች የውሽት ቋት ሙሉ በሙሉ በመናድና በማምከን የኢትዮጵያውያን ዐብይ የዜናና የመረጃ ምንጭ እንዲሆን ወያኔና የወያኔ የጎሣ ፖለቲካ ሰለባ የሆኑ ድርጅቶ፣ ቡድኖችና ግለሰቦች ከሚጠቀሙባቸው አዳዲስ ስያሜዎች ራሱን ሙሉ በሙሉ አጽድቶ ጥርት ያለ ጽኑ ኢትዮጵያዊ አቋም መያዝ የሚኖርበት:: ይህም ማለት በኢትዮጵያ ውስጥ በምንም መንገድ ይሁን ኦሮሚያ፣ አማራ፣ ሱማሌ፣ ወዘተ የሚባል አገር ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍሎች ተቻችለውና ተጋግዘው በሰላምና በእኩልነት ሊኖሩባት በሚችሉባት (በነገዋ) ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ውስጥ ሊኖር ስለማይችል የበፊት የክ/ሀገር፣ ከተሞችና ተቋማት ስሞች እንደ በፊቱ መጠቀም የወያኔን አዲስ የጎሣ ክፍፍል/ክልል አለመቀበል ብቻም ሳይሆን ወያኔና የጎሣ ፖለቲካ ሰለቦቹ በብቸኝነት የቀረጹት ሕገ-መንግሥትም ሕገ-ወጥ በመሆኑ ትግላችን ፍፁም ሥር ነቀል መሆኑን ጭምር አስረግጠን ማሳየት የሚኖርብን:
በእኔ የግል እምነት መሰረት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ከወያኔያዊ አቋማቸው መጀመሪያ ራሳቸውን አጥድተው ወጣቱ ትውልድ አሳፋሪ ለሆነ ጥቅም ሲል በወያኔ የጎሣ ፖለቲካ ሰለባ እንዳይሆን በአንድነት ፓርቲ ውስጥ “ምክር ስጭ አባት ሆነው” እንዲያገለግሉ ራሳቸውን ከሥልጣን እርካቡ ገድበው ቢሆን ኖሮ እጅግ በጣም በተከበሩ ነበር:: ይሁን እንጅ ‘ድመት መልኩሳ አመሏን አትረሳ’ ሆነና የአንድነት ፕሬዜዳን ሆነ ተመረጠ በተባለ ግዜ “ኢህአዴግ የአራት ድርጅቶች ግንባር ሆኖ እያለ ሥራ የሚሰራው ግን አራቱም ድርጅቶች አንድ ላይ ሆነው ነው” ብሎ ኢህአዴግ የአራት ድርጅቶች ግንባር እንደሆነ አድርጎ ግንዛቤ ለማስጨብጥ ይጥር ነበር:: ለመሆኑ የአገሪቷን ወታደራዊ ጠቋም፣ የመንግሥት የሥልጣን መዋቅሮች፣ የደኅንነቱን፣ የፖሊስ ተቋማትንና ልዩ ጥበቃ ኃይልን፣ ኤኮኖሚውን (ንግዱንና እርሻውን)፣ የአገሪቷ በጀት እየተባለ በይፋ የሚነገረውን ግን ደግሞ ወያኔ ብቻ እንደፈለገ የሚጠቀምበትን፣ የተለያዩ ሃይማኖት ተቋሟትንና የውጭ ኤምባሲዎችን፣ . . . ወዘተ ሙሉ በሙሉ የሚቆጣጠረው ወያኔ ብቻ መሆኑ እየታወቀ ለምንስ ነው ወያኔን ኢህአዴግ ብለን የምንጠራበት ምክንያትና አግባብ?
ከዚያም አልፎ ተርፎ ነጋሶ “የራስን ዕድል በራስ የመወሰን እስከ መገንጠል ድረስ ያለን መብት መቀበል ዴሞክራሲያዊ ጉዳይ እንጅ ልንቃወው አይገባም” እያለ ትንታኔ ይሰጥ ነበር:: እነዚህ የነጋሶ ጊዳዳ ትንታኔዎችና ግንዛቤዎች በቀጥታ የሚያሳዩን ምንም እንኳን ነጋሶ የአንድነት ፖርቲ ፕሬዜዳንት ሆኖ ይመረጥ እንጅ በፊት ከነበረው የወያኔ የጎሣ ፖለቲካ ሰለባነቱ ቅንጣት ታክል እንኳ ፈቅቅ አለማለቱን ነው:: እናም እኔን ያሳዘነኝ ነጋሶ በድፍረት ያን ማለቱ ሳይሆን በየትኛውም አህጉር ያለው ገራገሩ ሕዝባችን ወዳጅና የትግል አጋር ያገኘ እየመሰለው ወያኔ አላምጦ ለተፋው ሁሉ አጨብጫቢና አስተናጋጅ መሆኑ ነው:: እውን አቶ ገብረመድህን አርያን የመሰለ ቆራጥና ጽኑ ኢትዮጵያዊ ወገናችን እያለ አቶ ስዬ አብርሃ በኢትዮጵያውያን መድረክ ላይ በትርፍ ግዜው ተገኝቶ መለስ ገንዘብ እያሸሸ እንደሆን እንዲነግረን መጋበዝ ነበረበት – - – ሕዝባችን እሱ ባሰለጠነው በአጋዚ ልዩ ኃይል እየተጨፈጨፈ ባለበት እጅግ በጣም አሽቸጋሪ ወቅት??? አቶ ስዬ አብርሃ እኮ አገር እያጠፋ ያለውን የወያኔን ዘረኛ ሠራዊት መናድ ከፈለገ ብዙ ብዙ ስራ መስራት በቻለ ነበር:: እሱ ግን የወያኔ ጦር እንዲነካ አይፈልግም:: እንዲያውም ይህን ለማድረግ የሚፍጨረጨሩ ቢኖሩ ተገቢ እንዳልሆን ብዙ ብዙ ብዥታ ለመፍጥር ይሞክራል:: ዳሩ ምን ይደረግ እንደ ሌሊት ወፍ ሁለት ክንዱን ግራ ቀኝ እየዘረጋ (የስዬንና የነጋሶን ክንዶች ወደላይ በማንጠልጠል) አንድነትን ያፈረሰው ኢ/ር ግዛቸው ሰለሆነ ወጣቶች ነጋሶንና ስዬን ቢያሽቃብጡ አይፈረድባቸውም::
ሌላው ግን ምንም እንኳን ወያኔ በአገር ቤት በሕዝባችን ላይ እየፈፀመ ያለው ግፍ በደሉ ከሚፈፀምበት ሕዝባችን የተደበቀ ባይሆንም ቅሉ በደርግ ግዜ አገር ቤት ውስጥ የነበረውን ሁኔታ በስፋት በመዘገብ ረገድና ከዚያም አልፎ በመሄድ በወቅቱ ከደርግ ጋር ጦርነት ያደርጉ ለነበሩት ለሻዐቢያና ለወያኔ እንደ ቃል አቀባይ ይቆጠር የነበረው የአሜሪካ ራዲዎ ድምፅ VOA የአማርኛው ክፍል ዛሬ ዛሬ ጭራሽ ከጥቅም ውጭ እየሆነ በመጣበት ወቅት – - – እንደ-አብነት ያህል አልፎ አልፎ የሚደረጉ ቃለመጠይቆች እንኳን ሳይቆራረጡ ለአድማጭ እንዳይደርሱ በማሰብ የ5 ደቂቃ ቃለመጥይቅ ጭራሽ ትርጉሙን አጦ ስንት ግዜ እንደሚቀርብ አሉላ ቃለመጠይቅ ብሎ ጀምሮ ሰዎችን አስተዋውቆን ቀሪውን በሚቀጥለው ሳምንት ይዘን እንቀርባለን ብሎ በስልት ሸውዶን የሚያልፈውን፣ የዋልድባ ታሪካዊና ጽንታዊ ገዳማት በስኳር ልማስት ስም በወያኔ አደጋ ላይ ወደቁብን ብለው የገዳሙ አባቶች ለVOA ቃለመጠይቅ በሚሰጡበት ግዜ እጅግ በጣም ኃላፊነት በጎደለው መልኩ “ታዲያ መንግሥት አካባቢውን ለልማት የሚፈልገው ከሆነ ለናንተ ሌላ ምትክ የሚሆን ቦታ አልተሰጣችሁም እንዴ?” ብሎ አዲሱ አበበ ወያኔ ለቀደደው አፍራሽ ድርጊት ተባባሪ መሆኑንና ሄኖግ ሰማ-ሕ/ብሔር የሚባል VOA ዘጋቢ በG-8 የመሪዎች May 18, 2012 ሰብሰባ ላይ ተገኝቶ ያደረገው ቃለመጠይቅና ያቀረበው ዘገባ ሚሚ ስብሀቱ በነ ሞሶሎኒና ናዚ ዲቃላዎች ማካከል ተገኝታ በቆራጡ ጋዜጠኛና ወጣት ሙሁር አበበ ገላው ላይ ከሰጠችው ታሪክና ትውልድ የማይረሳው አሳፋሪ ድርጊት ጋር የማይተናነስ መሆኑን መስማት እጅግ በጣም አስነዋሪ ብቻም ሳይሆን አሁን በተቋሙ ((VOA) ላይ ያሉ ሁሉ (በራሳቸው ፍላጎትም ይሁን አልያም በሚደረግባቸው ጫና ምክንያት) ለኢትዮጵያ ሕዝብ ትክክለኛ ዜና እያቀረቡ ስላልሆነ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር በቀጥታ ከመጣላታቸው በፊት በምልካም ፈቃደኝነት ስራውን ጭራሽ እንዲተውት ወደምንጠይቅበት ሁኔታ እየተገፋን ባላበት ወቅት – - – ኢሳት/ESAT አስተማማኝ በሆነ መንገድ ለኢትዮጵያውያን ጠንካራ የዜናና የመረጃ ምንጭ ሆኖ እንዲቀጥል የፋይናስ ሃቅሙ ከቀጥታ ሙያተኛ የሰው ኃይሉ ጋር ተጣጥመው የሚሄዱበትን ስልት የኢሳት ማኔጅመንት በየግዜው ማገናዘብ ተገቢ ከመሆኑ በተጨማሪ በመልካም ፈቃደኝነት ላይ በተመሰረተ መልኩ በነፃ ግልጋሎት ሊሰጡት የሚችሉትን ተሳታፊዎችና የኢትዮጵያን ታሪክ የሚያውቁ አማካሪዎች (የሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል ተዋዕፆ ያለበት) ቢኖሩት እጅግ በጣም ይጠቅማል የሚል የግል አስተያየት አለኝ::
ምን እንኳን የኢሳት ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም ከአባ ኒቆዲሞስ ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ “ምናልባት ነግ ኦነግ በተመሳሳይ ሁኔታ ኦሮሚያን ቢያስተዳድር ሌላ ቋንቋ ተናጋሪ በሆኑ የሕብረተሰብ ክፍሎች ላይ ችግር አያመጣም” ወደ ሚል መደምደሚያ እንዲሄዱለት ለማድረግ መሞከሩ አሳዝኖኝ ግን ደግሞ የአንባቢያን ቀልብ ለመሳብ ይመቸኝ ዘንድ ግልፅ ደብዳቤ ለኢሳት/ESAT ልበል እንጅ ከላይ በተመሳሳይ ሁኔታ የተለያዩ ግለሰብ ስሞችን እያነሳሁ ችግሮችን ለማሳየት በመሞከሬ ኢሳት ተጠያቂ አይሆንም:: አጠር ባለ መልኩ ቀጥዬ ለማቅረብ የምሞክረው ግን በቀጥታ የኢሳት ታዳሚዎችን የሚመለት ይሆናል::
ባለፉት 21 ዓመታት የወያኔ አስከፊ አስተዳደር ውስጥ ተፈጥረው የነበሩ መልካም የትግል አጋጣሚዎች ነበሩ:: ሆኖም ግን ሁሉም እንደዋዛ ሳንጠቀምባቸው አምልጠውናል:: በዚህ ረገድ በዋና መልኩ ሊጠቀሱ ከሚችሉት ዋና ዋናዎቹ ውስጥ ወያኔ መላ አገሪቱን በ1983 ዓ.ም በተቆጣጠረ ግዜ በአገር ቤት ታማኝ በየነ ወጣት ኢትዮጵያውያንን አስተባብሮ ብዙ ቅርሶች በወያኔና ጀሌዎቹ እንዳይፈርሱ ሲከላከል በውጭው ዓለም ደግሞ ኢትዮጵያውያን በኢዴኃቅ ዙሪያ ተሰባስበው የተለያዩ የተቃውሞ ሰልፎችን ከማድረግ በተጨማሪ ኢዴኃቅ ወሳኙን ፀረ-ወያኔያዊ ትግል በብቃት የሚመራ መስሎ ይታይ ስለነበር ከፍተኛ ገንዘብ በየስብሰባው የተለገሰው ቢሆንም የኋላ ኋላ ግን ኢዴኃቅን ይመራው የነበር ግለሰብ ሱዳን በመጣ ግዜ ያንን ገንዘብ የተጠቀመበት በአባላቱና ደጋፊዎቹ ቆራጥ ጅማሮ ወሳጅነት ወሳኝ የትጥቅ ትግል ጀምሮ የነበረውን ማዘርላንድን ለማፍረስ ነበር:: ይህ ግለሰብ ሱዳን በመጣ ግዜ ከዚህ አሳፋሪ ድርጊቱ ተቆጥቦ ለኢሕአፓ አባላት ብቻ ሳይሆን ለሁላችንም አመራር በመስጠት ፀረ-ወያኔውን የትጥቅ ትግል እንዲያስተባብር ሻለቃ አጣናው ዋሴ ድንጋይ ይዘው አጎንብሰው ቢለምኑትም እሱ ግን ተልዕኮው አገርን አስተባብሮ ከማዳኑ ላይ ሳይሆን በአንድ ድርጅታዊ ስሜትና ዓላማ ተጠምዶ ስለነበር ልመናቸውን አሻፈረኝ ብሎ እጅግ በጣም አሳፋሪ ንትርክ በትግሉ ግንባር እንዲፈጠር በማድረጉ የሱዳን መንግሥት በሁኔታው ተገርሞና አዝኖ ይህንኑ ግለሰብ በ24 ሰዓት ውስጥ ወደ መጣበት እንዲመስ ሲያደርጉት እኛን ደግሞ በሂደት ለእስር ዳርገው ካቆዮን በኋላ በUNHCR ጣልቃ ገብነት ከአካባቢው እንድንለቅ በማድረግ ትግሉን እንዴት እንደጎዳው የሚያውቅ ያውቀዋል:: ሻለቃ አጣናው ዋሴ ግን ልጆቻቸው ውጭ እንዲወጡላቸው ቢለምናቸውም አገሬ ከወያኔ ነፃ ሳትመጣ ከአካባቢው አርቅም ብለው እምቢኝ ስላሉ ከቀሪ የማዘርላንድ አባላት ጋር ከሱዳን በወያኔ ታፍነው በቃሊቲ እስር ቤት ሕይወታቸው ሊያልፍ ችሏል::
ከዚያም ቀጥሎ ፓሪስ አንድ ፓሪስ ሁለት የሚባሉት በኢቶ-ኤርትራ ጦርነት ግዜ ከወያኔ ጋር ተደራድሮ ለመግባት ብዙ የጦርነት ቅስቀሳ በማድረግ የመሃሉ አገሩ ሕዝብ ወደ ጦር ግንባር እንዲዘምት በማደረግ እነ ስዬ አብርሃ ፈንጅ ረጋጭ አድርገው ሕዝባችን ካስጨረሱ በኋላ ‘ሕብረት’ ተብሎ ሲመሰረት በውጭ ያለው ኢትዮጵያዊ ወገናችን ትግሉ መልሶ ሕይወት የዘራበት እየመሰለው ገንዘቡንና ግዜውን ቤዛ ከማድረጉ ባሻገር በተመሳሳይ ሁኔታ ቅንጅትን መርዳት ማለት ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጎን እንደመሰለፍ ይቆጠራ ተብሎ ብዙ ገንዘብና ግዜ ያለብቃትና ሁነኛ አመራር ባከነ – - – በወቅቱ ለሁሉም ጠንካራ ድልድይ ሆኖ ያገለግል የነበረውና ብዙ ስራ የተሰራበት ተንሣኤ ራዲዎም ብዙም ሳይውል ሳያድር ልሳኑ ተዘጋ::
እናም ከዚህ መሰሉ ተደጋጋሚ ውድቀት ትግሉን ለማዳን የኢሳት ታዳሚዎች ኢሳት በሚያቀርበው ዜና ብቻ እየተቆጨን ከወሳኙ ትግል የምንሸሽ ከሆነ ኢሳትም ሕዝብን የማነሳሳት ጥረቱ ነግ እንደ ተንሣኤ ሬድዮ ሁሉ ከንቱ ሆኖ ይቀራል እኛንም ታሪክና ትውልድ ይፋረደናል – - – ሕሊናችን ይሞግተናል:: እዚህ ላይ አንድ በሚገባ መገንዘብ ያለብን በሕዝባችን ላይ የሚደረገውን ድርጊት አገር ውስጥ መልሶ ማቅረቡ ጉዳት ባይኖረውም በይዘቱ ግን ለቀባሪው አረዱት ነውና የኢሳት ሁነኛ ታዳሚ (Target Group) በሕዝቡ ላይ እየተፈፀመ ያለውን አበሳ ውጭ ያለው ወገኑ (የኢሳት ታዳሚ) እንዲያውቀው በማድረግ ከማንም በፊት ፊቱን ወደ ወሳኙ ትግል በማዞር አገርና ሕዝብን እንደዚያ ካለው አደጋ እንዲታደግ ማድረግ ነው:: ይህን መሰሉ የሰመረና የተቀናጀ የተግባር ሥራ የሚሰራ ከሆነ ኢሳት እስከመጨረሻው ድል ድረስ የትግሉን ውጤት እየተከታተለ ለሕዝብ ቢያደርስ ያምርበታል ለትግሉም ጠንካራ ድልድይ ሆኖ ያገለግላል:: ሕዝቡም ድጋፉን እስከመጨረሻው ለኢሳት ይሰጣል::
“. . . በጀሮህ አተኛ. . .”
ቋንቋ ፖሊስ (አጋዚ) ሆኖ – ከቀዬ አፈናቅሎ ካማሳው አፈናቅሎ
ጎሣ ፖሊስ (አጋዚ) ሆኖ – ከእርስት አፈናቅሎ ከቤቱ አፈናቅሎ
ሕዝቤ ክፋኛ ተራበ – አገሬ ጭምር
ብቃያው ደስ አይል – አውድማው ጭምር
መሬቱ ደረቀ – ደኑ ተራቆተ
ቀየውን አያውቁት አየር ጠባዩን
እርሻውን አያውቁት በሬ አጠማመድን – ሞፈር ቀንበሩን
ምርጥ ዘር አለን ብለው ነጠቁት የሱን- አጠፈት የሱን::
ጀማሪው (ቀያሹ) ኢጣሊያ – የናዚ ጓደኛ
ቀጣዩ ወያኔ ጥርቅም ምንደኛ – የነሱ ድቅያ::
ቴዎድሮስን ተዋቸው – አትቀስቅሷቸው
አሉላን ተዋቸው – አትቀስቅሷቸው
ምኒሊክን ተዋቸው – አትቀስቅሷቸው
ባልቻንም ተዋቸው – አትቀስቅሷቸው
በላይን ተዋቸው – አትቀስቅሷቸው
ጀግኖችን ተዋቸው – አትቀስቅሷቸው
ለአገር ክብር ሲሉ – ለአገር እድገት ሲሉ
ብዙ ጉዞ ሄደው – ተራራውን ወጠው – ቁልቁለቱን ወርደው
ደክሟቸዋልና አርፈው ይተኙበት አትቀስቅሷቸው::
ፋኖ ተጠራራ ጎበዝ ተጠራራ ጀግና ተጠራራ
ገፍተውናልና ከተውናልና ለአሳር ለመከራ::
አዋጁ ይነገር እምቢልታ ይመታ
ገና አይቀርለትም እሰከ ግባተሞቱ ባፍጢሙ እስኪደፋ
እንግዲህ ምን ቀረን አቤ ከገፈፈው – አቤ ከቀደደው
የቆፈንን አድማስ የፍርሃትና ሸማ – የውርደትን ካባ::
ስብስበውን ተወው አትሁን መለኛ
ማነብነቡን ተወው ከንቱ ጥበበኛ
ወይ እንደ ቅንጅት ግዜ የድል አጥቢያ አርበኛ
ወይ እንደ ስም-አይጠሬ መጥፎ ከዳተኛ
ወይ እንደ ሕብረቱ መንታ መንገደኛ
ወይ እንደ አመራረ ቢሱ የስልጣን ጥመኛ
መድረክ አይፈይድም አትሁን ዜዴኛ አትሁን መንተኛ
ሌላ መንገድ የለም ሌላ ዘዴ የለም አትሁን ከዳተኛ
ትጥቁን ሳታስፈታው ለፍርድ ሳታቀርበው ያነን ጎጠኛ
እንግዲህ ነቃ በል የአበበን ቃል ስማ – በጀሮህ አተኛ – በጀሮህ – አተኛ::
በቀን አስር ግዜ በቁማቸው ለሚሞቱ ለነሆድ ባምላኩ የፍርሃት ማስታገሻና ለአበበ ገላው ደግሞ ለክብሩ የስንኝ ቋጠሮ ትሁንልኝ!! – አንተነህ ሽፈራው!!



It is very sad to see abugidainfo be a mouthpiece of Moresh ( Amhara Union).
We Ethiopians have been subjected to one side of history of a long long time.
Moresh ( Amhara Union) just to remind you we Ethiopians have different culture , different life style, many beliefs , many languages and different kind of experience in history and off-course we have some common we might share. Ethiopia is for all Ethiopians not only for Amhara people.
Amhara people are one part of Ethiopia, BUT NEVER see Ethiopia as one part of Amhara!! Moresh ( Amhara Union) might wish for it. Moresh I hope you understand what it mean.
Peace and democracy for Ethiopia!!
I haven’t seen anything important in this article. Who cares about the losers EPRPs anyway? The fact is Ethiopians do not need any of the political organizations based on the outdated ‘Amhara’ ideology. We need something bigger than any ethnic dominance whether it is Amhara, Oromo, Tigre etc. Specially, the outlook of Amharas is by far more dangerous, divisive, backward and disgusting than that of EPRDF’s. Amharas did not do any better for the last 100 years rather than killing and humiliating the citizens. I am fine with weyane until we come up with a more progressive and all inclusive political movement. But, no power for the Amharas!!!!
brother thank you for sharing your fear. but the ethiopia’s people struggle is not to settle gada system in ethiopia. the gada system is far better than the tegere’s gujiles aparthiede system, but we are doing our best to put the foundation for true and geninue democracy on that lovely and anceint ethiopia. So do your share for the struggle to free our country and our people from narrow and shallow minded tegeres and their cos from china, india, turkey, pakistan and indonsia,
weregna nehe anetena yaneten mesayoche kemawerate besetekere le ethiopia hezebe meneme yemetametulet negere yelem.ye ethiopia hezebe mene enedemitekemewena mene enedemigodawe tenekeko yemyaweke asetewaye hezebe new bewere meneme enedemayegegne awekotale kemane gare enedemikomeme yawekewal.anetena meselocheh kehager wetetachehu meserate siaketachehu were menefate becha new serachehu.
በመረጃ ያልተደገፈ በግልጽ ጥላቻ የተጀቦደ በአመክንዮ ላይ ያልተመሰረተ እንቶ ፈንቶ ክመሆኑም በላይ ያልበሰል አዕምሮ ቅዠት:: አንብቡት!!
To the wanna be a writer,
1.Dr. Negasso knows Ethiopian history way better than you. Fact!
2.You dont even know how Geda system works. or may be that’s your own understanding…..read or ask before opening your blabber mouth otherwise people would label you as ‘retard’
3.I advise you to refrain from politics. you are immature, emotional and racist.
4.If you want a real democratic country , you should accept the fact that there are more than 75 ethnic groups in Ethiopia. Each is proud of their language.Oromiya is one of them who don’t even want to hear or speak amharic…you know that!
5.Geda system is the a system created by people who believe in democracy and unity….they are the OROMO people. too sad you are not OROMO.
Mr.Antneh Shiferaw, I did not under stand your article.You wrote many things .There is no topic a sentence and main idea.It is confusion and it is insulting some intelectual person.Excuse me i can not catch any point. It is endless in valid point ,please write the topic and main idea,even the predictor point.
What a rubbish and unscholarly article! Brother, good writers are good readers. It is clear that you lack the expertise how to put facts together. You are only an ignorant follower of your debtera fathers who have been writing myths as history in order to divide our country and create generational scars. If you can’t write the reality as it appears, shut your dirty mouth and let’s move on. Specially never talk or write about the Oromo people. I hate when Amharas talk about Oromo and their history. I can sum up your whole article in one statement; “little things affect little minds. “
@Peace Fo All
When you are told the truth you fail to understand. I think this article is based on facts. I appreciate such kind of individuals who tells the true. Thank you writer
It is really sad when stupid people like this writer get the chance to openly open their dirty mouth and spit their idiocy against our people. You don’t know about the Gada system because you have been hiding yourself behind the borrowed history from outside. Even if the Gada system has a problem, it is not shameful like the one you have been raised to which taught you how to beg on the streets. Under the Gada system, the Oromos were prosperous until the mad dog menelike arrived armed by the European colonialists. Do not feel ashamed about the Gada system because you have more than enough shameful stuff in your Amhara culture. We know each other very well so never try to rewrite your dirty history of the so called “3000 years”. A people who have that long history should be respectful and intelligent enough to consider other peoples’ causes. That is why we say unity with Amharas is a shame for the Oromo people.
አንተነህ ሺፈራው በአቀረበው ሃስብ ብዙ ቁም ነገሮች ይታያሉ::ከመሰርቱ የኢትዮጵያን ታሪክ እየዳሰሰ አሁን ያለንበትንም ችግር አብጠርጥሮ ያሳየ ነው::
ዘመናዊ የመንግስት አስተዳደር በአልተመሰረተበት ዘመንና አገር ሰዎች በቡድን ሁነው የራሳቸውን መሪ መምረጥና መምራትና መመራት የሰው ልጆች ታሪክ ነው::በአንዳንድ አካባቢ የጎበዝ አለቃ ይባል የነበረው ነው::የታሪክን ሰነድ ስናገላብጥም ይህን ነው የምናገኘው::ይህ ታሪክ የማንም ሳይሆን የስው ልጆች ታሪክ መሆኑ ታውቆ ቢታለፍ ይበጃል::
የሰው ልጅ አስተሳሰብ ዳይናሚክ( የሚያድግና የሚበልጽግ)ነው::ሰዎች ከስህተታቸው ተምረው ታሪክ ሊሰሩም ይችላሉ::
ቀደም ሲል አንዳንድ ሰዎች የስሩትንና የተናገሩትን ማብጠልጠሉ ወንዝ አያሻግረንም::አሁን ምን እየሰሩ ነው የሚለውን መመልከቱ ተገቢ ነው::በኢትዮጵያ ሰራዊትና በግብጽ በሚታዘዘው አብዱላሂ ሰራዊት የውጊያው አጅማመር ይህን ይመስል ነበር::የገና እለት አጼ ሚኒልክ በአሉበት ሰራዊቱ በዓሉን እያከበሩ እያሉ ለሊት ላይ የአብዱላሂ ሰራዊት በጠባቂ ወታድሮች ላይ አሰቃቂ ግድያ አካሂዱ::በዓሉን እያከበሩ የነበሩት ሰራዊት ራሳቸውን ለመከላከል ሲሉ ለ15 ደቂቃ ተዋግተዋል አሽንፈዋልም::በጦርነት መሞትና መቁሰል ያለ ነገር ነው::ይህ የጦርነት ታሪክ ከኦሮሞ ህዝብና ከአማራው ህዝብ ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም::የኢትዮጵያ ሰራዊት አማራ:ትግሬ:ኦሮም ሁሉም የተካተተበት ህብረብሔር ነበር::አሻራውንም መመልከት ይበጃል::
የጋዜጠኛ ፋሲል የጥያቄ አቀራረብና የሰውየው መልስ ከዛ ያለፈ መሆን አልነበረበትም::የሞቱት ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ነፍሳቸውን ይማር::ለወድፌት በታሪክና ስህተቱ እንዳይደገም ፈልፍሎ በታሪክ መዝገብ ይመዘገባል::
የገዥዎችና የቡድኖች ስህተት የህዝብ ስህተት አይደለም::ይህን መለየት ያግባባናል::ቡድኖች በስሜት ብዙ ወንጀል ሲፈጽሙ ማንንም አማክረው አይደለም::በዚህ አመለካከት ማየቱ ይሻላል::በቀል የትም አያደርስም::
የአንተነህ ሺፈራው አቀራረቡ ስህተቶችን እንዳደግምና ታሪኮችንም በትክክል ያስቀመጣቸው ስለሆነ ሊያስተምሩ ይችላሉ::
ከመሳደብና ከመራገም በጨዋ አስተሳስብ ሃስቡን መንቀፍና በተጨባጭ ማስረጃ ማቅረብ ይመረጣል::
አቶ አንተነህ ሽፈራው የምትናገረው ሀቅ ነው:: እኔም በበኩሌ በ ኢሳት ላይ ያለኝን አስተያየት በአድራሻቸው ለኢዲቶሪያል ክፍል ጨዋነት በተላበሰው አማርኛ ብጽፍላቸውም የተላከልኝ መልስ የስድብ ናዳ ነበር:: በጣም ነው የገረመኝና ያሳዘነኝ:: እች ባቄላ ካደረች አትቆረጠምም እንደተባለው ሁሉ እንደወያኔ ልሳን ማናባቱ ነው አስተያየት የሚሰጠን ከሚል ደረጃ እንደደረሱ ተገንዝቤአለሁ:: የኔ አስተያየት ጋዜጠኞቹ አንድን ሃሳብ ጭረው ለህዝብ ውይይትና ፍርድ ያቅርቡ እንጅ ራሳቸው ፈራጆች መሆን የለባቸውም:: በተለይ የአንድ ድርጅት ፍላጎትን ለማንጸባረቅ ጥረት ስለሚያደርጉ ጸረ ወያኔውን ኢትዮጵያዊ የአንድነት ሀይል እያገለሉ ነው:: ኢሳት ከድርጅት ልሳንነት አልፎ ሀገራዊ አጄንዳ ያንጸባርቅ የሚል አስተያየት ነበር የላክሁላቸው:: ያ ካልሆነ ኢሳት ገለልተኛነቱ ስለሚደበዝዝ በቀላሉ የምንመርጠውን ድርጅት ልሳን ማዳመጡ ይቀላል ብላቸውም ሙልጭ አድረገው የስድብ ኢሜይል ስለላኩልኝ እኔም በበኩሌ ዜናቸውን ላለማዳመጥ ማቀብ ካደረግሁ አንድ ወር ሆኖኛል:: ለነገሩ ከኢሳት ምን አዲስ ወሬ ላገኝ? ወያኔን ከሆነ ከነሱ የበለጠ ጫካ ሳሉ አውቃቸዋለሁ:: ወያኔ ከደደቢት አራዊነቱ በክፍለዘመንም ሊለወጥ የማይችል ስለሆነ ስለወያኔ አዲስ ነገር ያለ አይመስለኝም:: ለኢሳት የቅንጦት ቴሌቭዥን የሚወጣው ገንዘብ በጋምቤላም ሆነ በጎንደር ከወያኔ ጋር ለሚፋለሙት ታጋዮች መድሃኒትና ስንቅ ቢሆን የበለጠ ትግሉን ያግዛል:: 80% ኤሌክትሪክ የሌለው ኢትዮጵያዊ እንዴት ብሎ ነው ኢሳትን የሚከታተለው? ለሀገር ቤት ወገናችንስ በምን ሞራል ነው ስለወያኔ ከውጭ ሆነን የምንነግረው? ህዝባችን ዋናው የመከራው ገፈት ቀማሽ አይደለምን? በወሬስ እንዴት አድርገን ነው እስካፍንጫው የታጠቀን ወንበዴ የምናንቀሳቅሰው? ወያኔ የሚሰማን ከተግባራዊ ትግሉ ሜዳ ላይ ሚዛን ስንደፋ ብቻ ነው:: እስኪ አንዳንድ ድርጅቶች ለኮንፈረንስ ለሴሚናር እያሉ ለሆቴልና ለትራንስፖርት የሚያባክኑት ገንዘብ ትግሉ ሜዳ ላይ ቢውል አሁን ቢያንስ 50% የቤት ስራችንን ሰርተን ነበር:: በማይጨበጥ ህልምስ እስከመቸ እንኖራለን? ለምን ከራሳቸው ከወያኔና ከሻቢያ አንማርም:: በቴሌቭዥን አይደለም የደርግን ሰራዊት ያንበረከኩት:: በቀበሮ ጉድጓድ የባሩድ ጭስ እያሸተቱ እንጅ:: አሁንም ቀልዱን እንተውና በተግባር ትግሉ ሜዳ ለመግባት ልምዱና ፍላጎቱ ላላቸው ሀገር ወዳዶች ብንረዳ ይሻለናል:: መማር መማር አሁንም መማር…
Last Sunday I listened an interview in Amara Union (Moresh) paltalk room, Aba Niqodimos. I have never heard a racist man like Aba Niqodimos in my life. The day I listened his interview I regretted giving menequses a big respect in life before. Starting from that day I understood that a menequse can be the worst creature. Let alone a menequse I never seen an ordinary individual being so discriminatory to others. This menequse (Aba Niqodimos) is a shame to the Ethiopian Orthodox church. I hope the head of the church will not entertain people like him in the title of menequse.
This writer might be him or his disciple.
God Bless Ethiopia!!!
My friend Anteneh, your hate didnt bring anything for the last 100 years, amara are as poor as oromo people. Nothing changed. Melese is also following the same hate driven superiority mind set and I am sure nothing will change for Tigray people in general.
About the article, it was published in 1980 (most probably around the time OLF strengthed) and The article you have quoted tells about 15th, 16th century but published in 1980, do you see something here?
1. Can I suspect that it was dergu propoganda to tell us, oromo has no country therefore no demand for thier birth right. It is very sad how you people mind thinks, thanks for your leadership, we reached 10 million hungery people, no country in the world used hunger as a weapon of control and shame on you. This time ofcourse Melese but you know who did it before him.
2. The funny author you have quoted might have lived 400 years to witness and write this article about Oromo each and everything and publish it in 1980, or he sow it in his dream both are possible in 3000 year history of retarded abysinian debtera’s, Get lost!!!
3. Ethiopia is Kush and doesn’t belong to anyone but to the Kush, like Oromo, Afar, Somali, Kambata, Hadia, Walayta, Agaw proper, Agaw who wanna be semetic and the line of king Solomon(Tigraia and Amara speakers)(ofcouse you guys are one of us until you claim, the solomon line to humilate the Kush Ethiopia and rule over them by force without democracy.
see Melese and Isayas what they are doing in Somalia. Insteed of helping that country as part of kush nation (of course they are somalia now), they used somalia as a strategy to stay longer in power. Mengistu did the same, why you guys dont work for freedom and democracy of all than domination?
4. Kush Ethiopia will survive not with people who hate themselves like you and Melese, who wann be others and work for the wests, but by the blood of the true kushites, but by true sons of freedom and humanity loving people of all kind in the horn. I hope such leaders will come out one day but till then let us dominate kill and humilate eachother.
Mr. / Ms. dhufu,
You may spit your little mind but nothing further from truth. The article is not about which clan is better or smarter. It is all about humanity supercedes kin, clan or ethnicity. I don’t know for which school of thought you belong to. But I know much of the Diaspora (regardles of ethnicity) is against the TPLF ethnic bantustanization. If one hates TPLF ethnic divide and rule, by the same token one has to condemn those narrow nationalists whereever they may be. We hate TPLF not because they came from Dedebit, it is their weired retarded defnition of human dignity as a function of one’s ethnic background. The 22nd century world can’t afford to be reduced to a mere fantacy of Zemene Mesafint or Samurai (Japanese) feudal world outlook. In japan I am a dignified person as much as any Japanese in front of the rule of law. None of my ethnic background is essential for what I am willing to choose. I have the fullest right to travel, make a living or do whatever I think whether in Hokaido, Tokyo or Okinawa regardless of my ethnic background, for that matter my citizenship. If Japan has been ruled by Samurai world outlook, I would naver been allowed to set a foot in the first place. You ought to know that your ethnic perspective is going to deny me that God given freedom and will also deny you as much as I am. Do you have the faintest idea of the fire you are playing with?
To my surprise, people like you are living with freedom and liberty in a far away country even your grandfather never heard of. Yet, you are stirring ethnic tension in your own country! What a miserable little mind you are?
Notice:
#10 Wako is different from me. I am ዋቆ in #12 and #15. Don’t misunderstood me.
I think the writer of this article has put so many facts. In fact he had started with the ESAT problem but all the name he had mentioned are pushing the same ideology. So, how comes one say the Gada system was better than the then Ethiopian system of Government? I think it is too late to know what a Gada system is. I myself half oromo and have amara but do not accept the Gada system better than the then Ethiopian rulers. Please read books books . . . historical facts. The problem is that H/Selassie had refused to teach Ethiopian history. Because he thought that if the Oromo knows their history, the history of raiding others, then they may not participate fully in the rebuiling process of Ethiopia. Most historians were speculating that if the oromo do not know the true history of their background could be claiming so and so. It is very sad to see that had happened in Ethiopia and killed so many innocent Ethiopians by collaborating with TPLF. This is very sad in this modern political era. TPLF, OLF & and their collaboraters will be facing justice. This is very important. We need new way of thinking so that we live together peacefully and democratically. Our aim is not to replace TPLF with OLF. So, this man always writes a very important issues, and I like to read his article. Because his stand is always constistance. His aim is not to replace TPLF with Amara or the so-called oromia. He always believe democratic Ethiopia. So, I thanks for his insight article.
አንተነህ;
ግራ የገባህ ይመስላል:: የቱን ወቅሰህ – የቱን አንደምትጥል ቸግሮሃል:: ለመሆኑ ማን ቀረህ? የኦሮሞ ከተሞቸ ስም: የኦሮሞ ታሪክ: የኦሮሞ ምሁራን: የኦሮሞን ታሪክ ያሞጋገሱ ምሁራን ሁሉ ውሸታችሁን ነው አልካቸው::
ለመሆኑ ጃፓን አገር በስደት ተሰቃይቶ መኖር አንዲህ ያበደ ውሻ ያደርጋል? ባለፈው የስፖርት ዘጋቢ ሳለህ አኮ ጎበዝና አሪፍ ነበርህ:: ወይ ወንድም አንተነህ ምን ክፉ ገጠመህ?
ሁምቦ
Dear Gemeda, There is a good old saying in Oromifa.
“Harka abbaa tokkotin ibidda quabbaachuun nama hindhibu.”
The meaning is “with somebodies hand it may not be difficult to catch a fire”. We have to understand we in the Diaspora are playing a fire at the expense of poor Ethiopians back home. These ethnic slurr or instigation will not benefit anybody – as it is backward and futile. We have to acknowledge every practice has its own difficiencies and strengthes. Therefore, whether it is from East or West, North or South it should be scrutinized, evaluated and appraised. Since our culture and practices are the products of our level of intelligence and development. Nothing is stagnant. Everything is subjected to contineous change. Our world has gone through many transformations. From the communal society to the slavery, feudal, industrial capitalist, technological and information age. Throughout these transformations cultures and norms are also transformed from local to national and international one. No country had democratic system in the 18th century but now it is a buzz word and symbol of sophistication.
Therefore, whether Gada, Idir, Debo, Wonfel, whatever are essentially subjected to contineous transformations. Practices and norms may born at some level of societal development, grow and serve as long as they are useful for that particular generation. When they are no longer useful they will cease to exist and eventually be replaced by a progressive one suitable for that society. We can not adminster justice like what our grandfathers did under the tree with out civil, criminal or commercial code. We are changed a lot than our grandparents. This transformation is healthy and a dialectical growth. Therefore, the discussion should not be a point of contention, instead civilized discourse to reflect upon. Gada has been serving the Ethiopian people pretty much in its time. And like all other cultures and norms it is subjected to transformation. With the information technology and the ever shrinking world laws and practices are getting internationalized as the same time working across the borders.
The downfall of Taliban in Afganistan is mainly attributed to their regressive attempt to bring 15th century in the 21st century world. Regrattably, in their short lived administration, they reduced their country atleast 2 centuries back.
Bear with me that I am not an advocate of scrapping all what we own before. But building on what is good and replacing obsolete practices with up-to-date ones. For example we have had a long tradition of circumcising girls which is detrimental to their health. Should we have to continue practicing for the sake of preserving tradition? Absolutely not.
With all due respect for you, we have to be tollerant, act by reasoning than impulse, and be open for dialogue even if we feel something is offending. What makes us different from other animals is not because we speak structured language but we are guided by logical reasoning. Without friction we would have never had been discovered fire which set a milestone for human development. Let’s have ideal frictions to bring about a result that will be beneficial for all humanity. We!!!
Yours, ዋቆ ዘአጋሮ
@Gemeda
Mr Gemeda, when it comes to the oromo people history you said it is too late to know what a Geda system is. But when it comes to your real identity you accepted it as it is and claimed that the then Ethiopian rulers as being good with out questioning.
Mr Gemeda next time please come up with your real identity, this time it didnt work out. Mr Gemeda you shouldnt be ashamed of who you are so dont hide yourself.
I always wonder why some people have parked there mind hundreds of years back to Minilik”s time. When the oromo people and other people question about Minilik leadership the ones who parked there mind argue that Minilik built roads and transportation and so on kkkkk.
With that poor argument we should support and praise weyane for bringing internet , mobile technology and so on kkkkkk.
No no no , but that is not the case we dont support weyane or Minilik”s leadership, let alone Minilik”s time even today there are human right violations in this 21 century. A human right violations in the past and today are not different , the style of violation might be different. Once you violated it, it is a crime.
So for all individuals who have parked in Minilik”s time , try to upgrade that parked mind and never try to defend undemocratically elected leaders of the past like Minilik.
As far as there are individuals who keep praising or worshiping Minilik there will be people to reject him. And with that we wont be united. By the way I used to listen tedy Afro songs but with his new album tikur sew , I am a little bit suspicious about his song for Minilik, hmm who knows weyane might be at the back. And we never know the deal to free tedy from jail.
So let as say RIP for Atse”s and move forward!! It is only weyane who benefit from division among us.
God Bless the cyber generation!!
በመጀመርያ ደረጃ ሊሳት ያለኝ አድናቆት ቃላት እያጠረኝ ነው የምገልጸው በተለይ አቤ ጀግናው ያን መለስ ድሮ ከጫክ እንደመጣ የነበረወን መልኩን በደቂቃ መመለሱ ደንበኛ ጦጣ አስመሰለው ዪትዮጲያን ህዝብ ድምጽ ነው የተነፈሰው እናም በመንግስታት መሃል ማስኩን ግለጠበት ታሪክ ከታሪክም በላይ ነው አቤ የኢትዮጲያ ህዝብ አንጀቱ ነው ቂቤ የጠጣው ወያስኔ ቡችሎቹንም ትንሽ አንጭረጨረከው. ከዛ በመቀጠል ይህን ጽህፍ በጻፈው ሰው ላይ ትዝብት አለኝ እኛ ችግራችን የማይገባኝ ነገር ወያኔ ማስኩን እይገለጠ የወያኔን ተንኮል እያጋለጠ ለእዝብ እያቀረበ ያለ ሚድያ ነው ለምንድነው ሁል ጊዜ ወያኔን ግራ እይጋባ እራስ ምታት ሆኖበትጥሩ እይተንቀሳቀሰ እያለ ለምን ድነው አቃቂር እያወጣችው ለማሰናከል የምትሞክሩት???????????????????????????????? በጣም እይገረመኝ ያለ ነገር ልደቱ ክህደቱን በተመለከተ አንድ ነገር የሚል የለም ክቡር ዶክተር ብርሃኑን በተመለከተ ግን ልክ ወያኔን ተቃዋሚ መስለው ይመጡና ትግላችወን ያንቃሽሻሉ የገባው አሪፍ መልስ ሰቶ ያዋረዳችዋል ያልገባው ደሞ የሸወዳል እኔን በጣም ይገረመኛል ይህን ጽሁፍ የጻፈው ለኔ ወያኔ ነው ኢሳት እይሰራ ያወን አንተ ሰርተሃል ወገን ሊገባን የሚገባ ነገር ቢኖር ማንም እዚህ ለሚለቀልቀው ዽጽሁፍ ቦታ መስጠት የለብንም አይለኛ ወያኔ የሚቅወሙ እና እንደአቅም እና እንድሙያቸው የሚንቀሳቀሱትን ለምን ትችት ይበዛል????????????ይህቺ የወያኔ ታክቲክ ነች ወይግድ ብዬሃለው አስመሳይ ደሞ የተቸከው እወነተኛ አንቲ ወያኔዎችን ነው ስለልደቱ ምነው ምንም አላልክም?????? አታምታታን .በተረፈ የወገኖችን አስተያየት አንብቤያለው አትሸወዱ ወያኔ ለሚሰጠው አስተአይየት ቦታና ስፍራም የለኝ ወገኖች ግን ይህን የወያኔ ታክቲክ መሳት የለብንም በተረፈ ለዋቆ ጥቂት የምለው አለኝ. አስተያቴን ኢሳት አልተቀበሉም ብለህ ይህቺ ባቄላ ካደረች ብለሃል አንተ ራስህ አስቤን አልተቀበሉም ብለህ ለኢሳት የሚወጣው በጋምቤላ እና በጎንደር ለሚታገሉት ገንዘቡ ቢወል አልክ????? ጋምቤላ እና ጎንደር ፍልሚያ እንዳለ በወያኔ ቲቭ ነው የሰማከው??????? በኢሳት ነው አገር ውስጥ ያለወን ችግር እና ነገር የሚነግረን ኢቲቭ አይደለም ቭኦኤ አይደለም አሜሪካ ድምጽ በጣም ከፍራት የጽዳ አይደለም ታውቃለህ ኢሳት ግን የማንም ጥገኛ ያልሆነ ነጻ ሚድያ ነው ወያኔ ኢሳትን ስንቴ አፈነ ?????? ለምን ይመስላህልላስፈላጊነቱን እና ህዝብ ክህዝብ እንድሚያገናኝ ስለሚአውቅ ጉዱን ስለሚያወጡ ትልቅ ፍራት አለው እናም አንድ ነግር ቢደረግ ሚድያ ወሳኝ ነው አለዛ በምን ታውቃለህ????? ወያኔ ሊነግርህ????? ሚድያ ወሳኝ ነው!!!!!!!!!!!!! እጅግ አስፈላጊ አስፈላጊ ነው!!!!!!!!!!!!! ለወጥ ያለሚድያ አይመጣም በተለይ ባሁን ሰሃት አማራን እና ኦሮሞን ለማጥፋትይ በታቀደ ጊዜ ወያኔ ተራ በተራ አንድ ነገር ቢያረግ ማን ነው የሚነግረን?????? የውጭ ጋዜጠኛ እና የአገር ውስጥ ጋዜጠኛ ዘልቆ መግባት እንደማይችል ታውቃለህ ይልቅ ከምንጊዜውም በላይ ኢሳት አስፈላጊ ነው.አኪልዳማ የትባለወን ፊልም ኦነግ ያረዳቸው ተብሎ ወያኔ ቆርጦ ያቀረበወን ፊልም አይተሃል ታማኝ በየነ ግን ኢሳት ላይ ኦነግ ሳይሆን ወያኔ እንዳረዳቸው የሰወይወን ቃል እነሱ የቆረጡትን ሙሉ ፊልም አጋልጦ ወያኔዎችን ጉድ አረገ የአዲስ አበባ እና ሁሉም ህዝብ ኦነግ ላይ ሲያግረመረም በዋላ እድሜ ለታማኝ ወያኔ መሆኑን አጋልጦ ህዝቡ ለዘላለም እንዳይማናችው አረገ ድሮም ወያኔ አይታመንም ያ ፊልም ግን ኦነግን አስጠቁራለው ብሎ እራሱ ጠቁሮ ቀረ ይህ በማን ተጋለጠ ??? በኢሳት!!!!!!!!!!!!! ያ ባይሆን ኦነግ ነፍሰ ገዳይ ትብሎ ክህዝብ በተተፋ ነበር አየህ?????? ብዙ ብዙ ነገር አለ መድረኩ አይበቃም ሁሉ ቢጻፍ አሁን በቅርቡ የፓርላማውን የስድብ አረበኛ መለስን እንደዛ አይጥ ሲያስመስለው ማን አጋለጠ????? ኢሳት!!!!!!!!!!!!! ህዝቡ በየአገሩ እንዴት እንድተደሰተ እናም ዋቆ ወንድሜ ኢሳትማ ቁጥር አንድ ነው!!!!!!!!!! አይደለም ገንዘብ ደምስ ቢሰጠው?????? እና አቶ አንተነ ሽፈራው እዚህ ደም እይፈሰሰ ህዝብ እያለቀ ነው አንተም አታምታታን ለሁሉ አቃቂር አወጣህ አንተስ ምን ሰራህ??ልህዝብ ማለቴ ነው ለግልህማ ተቆራጭ አለህ.በእውነተኛ ተቃዋሚዎች በኢሳት በግንቦት 7 በሌሎችም ቀልድ የለም አንተም የሃቅ እንጀራ ይሻልሃል.
ወንድም አንተንህ ብዙ አነጋጋሪ የሃገር ጉዳይ እያለ በሚድያ ላይ ጊዚህን አባከንከ በቆራጥ ታጋዮች ላይ አጉል ቅስቀሳ ከጀለህ ምነው ወደ መለስ ጎራ መቁለጭለጭ ጀመርክ እንዴ አደብ ግዛ ሃገር ይበልጣል ሆድ ያሳፍራል
ለመሆኑ ያለፈው ምን ያረጋል. ወደ ፊት እንደ ማንደላ
what a non sense long and disguising article that has no tail or horn but focus on personality rather than addressing points which the writer is either a weyane cadre or someone who is anti ESAT who is showing a crocodile tear in order to advance his prejudiced and hateful message, i think abugida should not give any place for a non sense staff
ነህማ ትልቅ ነገር ጠቀሽ. ዋቆ በምትሰጠው አስተያየት ብዙ ጊዜ አሳብህን የምጋራ ሰው ነኝ. እዚህ ጋር ነሂማ የልቤን አወጣችው እናም መድገም አልፈልግም የጎንደረን የጋምቤላን የአፋርን የሌሎችንም እንቃስቃሴ የሚያሳውቀን እኮ ኢሳት ነው ቭ ኦ ኤ ቁጥብ ነ ብዙም ነጻ አይደለም ኢሳት ግን ነጻ ነው ሁሉን ነገር የምናውቀው በዚህ ነው ድህና አረጎ ወያኔን እያስበረገ ያለ ሚድያ ነው . የወያኔ ተንኮል ሊገባን ይግባል ቢያንስ ፊደል ቆጥረናል ብዙ የዋሆች በቀላሉ የመሸወድ ጭንቅላት ይዘን ነው ወያኔ እድሜወን እይራዘምን ያለነው አሁን ወያኔ በባዶ ሜዳ ብቀላ ይዟል እንዲመቸው ደሞ የኦሮምን እና የአማራን ህብረት አይፈልግም እድሜው ቶሎ ስለሚያጥር እናም የኦሮሞ ህዝብ ብዙ የዋህነት አታብዙ በቀላሉ አትሸወዱ አሁን ይህ አንተነህ ተብዬ ወያኔ ነው እራሱን ወያኔን ተቃዋሚ አስመስሎ ቀረበ ከዛ ተሸውዳችው አሁን እስቲ አስቡት ኢሳት የሚታማ ነው??????? ??? ግንቦት 7 የሚታማ ነው??????? ስንት የኦሮሞ ጀግኖችስ የሚታሙ ናቸው?????? ይህ ወረኛ እንደዜጋ እሱ ምን ሰርቶ ነው?????????????????? የፈለገ ወያኔን ተቃዋሚ መስለው ቢቀረቡ እና አይለኛ ተቃዋሚ እና ለወያኔ እራስ ምታት የሆነን ሰወም ሆነ ድረጅት ከወቀሱ እና ክህዝብ ለማሸሽ ሲሞክሩ ያ ሰው ወያኔ ስለመሆኑ ምንም አትጠራጠሩ. ዘዴው ወያኔ ያው የታወቀ ነው ህዝብ አይደግፈወም አይወደውምም ትግራይ ውስጥ እራሱ የሚጠሉት አሉ እናም ለወያኔ ውጋት የሆነን ሰው ሁሉ በትቻላቸው ቀዳዳ በፕሮፓጋንዳ ማዳከም ነው ጦር ባንወጣ እንኳን ይህን ወረኛ ማሳፈር ያቅተናል??????? እጅግ አዘንኩኝ እዚህ ሚድያ ላይ ይህን አስመሳይ የትቃወማችወ ሁሉ አድናቆቴ ይድረሳችው. ዋቆ እስካፍንጫው የታጠቀን ሰው ወሬ አይሸንፈወም ሚድያ አይስፈልግም ላልከው ካንተ አይጠበቅም አለማዋጣት ትችላለህ ነገር ግን ሚድያ ቁጥር አንድ ነው. አገር ውስጥ ጄኖሳይድ በግልጽ ቢጀመር እንኳን ማን የሚያጋልጥ ይመስልሃል ???????? ኢሳት ብቻ ነው!!!!!!!አትሳሳት አስቤን አልተቀበሉም ብለህ እንዲህ ማለትህ በብኩሌ በጣም አስቆኛል. ኢሳቶች የራሳችው መመርያ አላቸው .በርግጥ ነጻ ሚድያ ነው እንዲህ እንዳንተነህ አይነቱ አስመሳይ እንዳይሸወዳቸው በጥንቃቄ እና በብልሃት ነው የሚሰሩት ቀላል ሚድያ እንዳይመስልህ ወያኔ ስንቴ ለማፈን ሞከረ?????? አሁንም ጄኖሳይድ በስወር ጀምሯል በግልጽ ደሞ ኢሳትን ፈራ!!!!!! አየህ ኦርጬወድሜ እንደወም እኔ ከዚህ በዋላ ለመርዳት ቆርጨ ተንስቻለው እድሜ ለአበበ ገላው ኢሳትን ሞር እንድወድ አረጎኛል ይህ ነው ሚድያ ኢሳቶች መለስ ጭራወን የተያዘች አይጥ እስኪመስል ድረስ በደንብ ያይነው እኮ በኢሳት ነው አገር ቤት ስደወል መርካቶ ያሉት ነጋዴ ዘመዶቼ የተሰማቸው ደስታ ይህ እው የሚባል አይደለም ሁሉም ኢትይኦፒያው እጅግ ነው የተደሰተው ያን ክፋታፍ የፓርላማ ውጭ የሚጠብቁትን ሰራዊት ተማምኖ በሰው ጡንቻ ቁጭ ብሎ ፓርላማ ጨዋ ተቃዋሚዎች ላይ ዋልጌነቱን ሲያንጽባረቅ አፉን ባሏን እንዳየች ሴት አፉን ሲከፍት አቤ አንገቱን አስደፋው የገዛ ደጋፊዎቹም ስቀዋል እውነተኛ ደጋፊውቹ ሳይሆኑ በገንዘብ የተገዙት ብዙዎቹ ነው የተረቡት እናም ምድያ ወሳኝ ነው. አቶ አንተነህ ህሊናህን አዳምጥ እወነተኛ ተቃዋሚዎች ላይ ወያኔ ለምን እንደሚያሰማራችው እናውቃለን አታቀርሻብን.
Esat is for ginbot 7 ginbot 7 is a stooge of Shabia .Shabia is creater of woyane . Thus woyane and G7 are brothers engaged in less serious conflicts on how to be big time darling of shabia.
አቶ አንተነህ አበበ ገላው መለስን ባዋረደበት ማግስት ምነው እሳትን ልትዘልፍ ወጣህ???????? ወገኖች አትሸወዱ ባካችው ወያኔን ሰድቦ ቢቀረብ ማስመስል መሆኑን አትዘንጉ አንደኛ እጅግ የተንዛዝ ሙዝዝ ያለ ጽሁፍ ነው ለማሳመን ደሞ ብዙ ጭረሃል የሚገረመው ደሞ አይለኛ የወያኔን ተቃዋሚ ነው ያማከው በል ባክህ አትቃዥብን. በኢሳትማ ቀልድ የለም ጌታህን አርበድብዶልናል እናም ወገን አትሸወዱ. እውነት አንተስ ምን ሰርተህ ነው ሌላወን ለመተቸት????? ባይሆን ስለልደቱ ጀባ በለን.
ውድ ነሂማ:
ስለ አስተያየትህ / ሽ አመሰግናለሁ:: የሆነ ሆኖ የተለየ ሃሳብ ያቀረበው ሁሉ የወያኔ ተላላኪ ነው ብለን የምናስብ ከሆነ በሳይበር ስፔስ ያገኘነውን የመናገር መብት አድማስ ያጠበውና እኛም ራሳችን የምንቃወመውን የወያኔን አፈና በራሳችን እንደመድገም ይሆናል:: ለመሆኑ ወያኔ ወያኔ እያለ የሚደነፋው ሁሉ ከወያኔ ነጻ ለመሆኑ ምን መረጃ ያቀርባል? እንደኔ አመለካከት ከሆነ ይልቁን ወያኔ የሚፈልገው ርዕስን በማስቀየር ቁምነገሩ ላይ ተከራክረን የነጠረ አቋም ይዘን እንዳንወጣ የተለመደውን ወያኔ ወይም ሻዕቢያ የሚል ልብወለድ ስም በመለጠፍ አዲስ ሃሳብ አፍላቂዎችን ለማስበርገግ የሚደረግ ዘመቻስ ቢሆን? ውይይቱን በ independent critical thinking ሳይሆን በ mass consciousness እውር ድንብሱን እንዲመራ የሚደረግ ሴራስ ቢሆን:: ለዚህ ደግሞ ብዙ ተመክሮ አለን:: ወያኔ ርካሽ የፖለቲካ ትርፍ ለመሸመት ሀውዜንን ያስደበደበ አረመኔ ለመሆኑ የማያውቅ ካለ ገና ሱሪውን አስተካክሎ አልታጠቀም ማለት ነው:: መራራውን እውነት እንነጋገር ከተባለ እሳት የአበበ ገላውን ተቃውሞ ወይም ሌላም ሌላም ዜና ቃረመ በትግሉ የሚፈይደውና አንድ ጋት የሚያስኬደን የተለየ ነገር የለም:: ሚዳቋ ዘላ ዘላ ከመሬት እንደሚባለው ነው:: ለምን ቢባል የወያኔው አምባገነን በአንድ ወቅት (ከ10 አመታት በፊት እንደተናገረው) በሪሞት ኮንትሮል ዲያስፖራው ካንቀሳቀሰን እናያለን ያለው አሁንም ልንሸሸው የማንችል መራራ እውነት ነው:: ይህ የሚያስረዳው ዲያስፖራው ወያኔን ማን እንደሆነ ገና አላወቀውም የሚል ነው:: ለዚህ ነው ይህ አካሄዳችን እንደማያዋጣን የተረዱ ወገኖች እየተነሱ ኣረ እባካችሁን እየተስተዋሉ ሲሉ የተለመደውን ወያኔ ወያኔ እያልን ለመማማር የተዘጋጄውን መድረክ ባፍ ጢሙ የምንደፋው::
ድክመቱን የማይገመግም ትግል ውድቀቱን ለመተንበይ ሳይንቲስት መሆን አያስፈልግም:: ለአበበ ገላው ያለኝ አክብሮት እንደተጠበቀ ሆኖ እሽ መለስ ዜናዊን በአደባባይ ዲክታተር ነህ አለው:: ታዲያ ምን ይጠበስ? መለስ ወይም ጋባዦቹ ዲክታተርነቱን አጥተውት ነው? ምን አዲስ ኢንፎርሜሽን አለና ኢሳት ባይኖር አናውቀውም የሚባለው? መልስን ዲክታተር ነህ ከማለት ባሻገር ከዲክታተርነቱ ለማስፈንጠር ምን ሰንቀናል? ይህንኑ ኢሳት ሊያመላክተን ይችላል ነው ጥያቄው:: መልሱ እስካሁን ምንም!
እኔ በበኩሌ ኢሳት የተወሰኑ ቡድኖችን ገጽታ ለማሳመር የተዘጋጄ ሚዲያ ነው የሚለው እምነቴ እንደተጠበቀ ሆኖ ከኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት ጋር ስናነጻጽረው የስርጭት ስፋቱ ከዚህ ግባ የሚባል አይደለም:: እኔ የምከራከረው cost benefit analysis በመስራት እንጅ በደመ ነብስ አይደለም:: እርግጥ ነው መረጃ ለትግሉ አንቀሳቃሽ ሞተር ነው:: ይህንን ሀቅ ማንም ሊዘነጋው አይችልም:: ይሁን እንጅ መረጃ ለማን እንዴት ስለምን ወዘተ የሚሉ ቁልፍ ጥያቄዎችን ሳንመልስ ቴሌቭዥን መስኮት የቀረበው ሁሉ አስፈላጊ መረጃ ነው ማለት የግንዛቤ እጥረት ምልክት ነው:: ቀደም ሲል እንደገለጽኩት መረጃ የሚሰበሰበው ለተግባራዊ አድራጎት የሚውል ከሆነ ብቻ ነው:: የኢሳት መረጃም የሚደርሰው ለዲያስፖራው ብቻ ነው ለማለት ይቻላል:: የዲያስፖራው ሚና ግን የአጋዥነት እንጅ የትግሉ ዘዋሪ ሞተር ሊሆን አይችልም ሆኖም አያውቅም:: በስታስቲክስ በተደገፈ መረጃ ለመነጋገር ከተፈለገ በቅርቡ በወጣ የወያኔ ሪፖርት የ ኤሌክትሪክ ሽፋን በኢትዮጵያ 40% ደርሷል ተብሏል:: በጣም ለጋስ ሆነን የወያኔን ሪፖርት እንመን ከተባለ ምናልባት 30% ኢትዮጵያዊ ኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ሆኗል እንበል:: ከዚህም ውስጥ አሁንም ለጋስ ሆነን 5% የሆነው ኤሌክትሪክ ተጠቃሚ የኢንተርኔት መስመር አለው እንበል:: አሁንም ለጋስ እንሁንና ከዚህ ውስጥ 3%ቱ መስመር ለወያኔ ደጋፊ ላልሆኑ ተሰጥቷል እንበል:: እንግዲህ ቸር ሆነን ወያኔ ሳያፍነው ኢሳት ለ2% ኢትዮጵያውያን ይድረስ እንበል:: ታዲያ እውነቱ ይህ ሆኖ እያለ የኢሳት ውጤት በጅ የሚዳሰስ ነው ብለን ለመንገር ያስደፍራልን?
አሁንም ደጋግሜ እንደገለጽኩት ሚዲያ አያስፈልግም አይደለም የኔ አቋም:: ሚዲያ ከሆነ ሰፊ ሽፋን ያለው ይሁን ነው:: ለምሳሌ ሬዲዮ አብዛኛውን የኢትዮጵያ ህዝብ ሊያዳርስ ይችላል:: ወጭውም የቴሌቭዥንን አንድ አስረኛ አይበልጥም:: ይህ ማለት ለአንድ ሰዓት የምናወጣው የቴሌቭዝን ፕሮግራም ለአስር ሰዓት የሬዲዮ ሽፋን ወይም በአስር ቁዋንቋዎች ለአንድ ሰዓት ዝግጅቶችን ለማቅረብ ያስችላል:: ውጤቱም የበለጠ ኢትዮጵያዊውን በየቀዬው ማዳረስ ይችላል ማለት ነው::
ከዚህ በተጨማሪ ባዶ ወሬ ሳይሆን ትግሉ ውስጥ ገብተው የሚፋለሙትን ወገኖች ማበረታታት መድሃኒት ማቅረብ ስንቅና ትጥቅ ማቀበል የበለጥ ትግሉን ምሉዕ ስለሚያደርገው ከቴሌቭዥኑ ወጭ ተቀንሶ ለተግባራዊው ትግል ቢውል ሬዲዮውም የተፈጸሙትን ገድሎች እየዘገበ በወያኔ ሰራዊት ሽብርና በጸረ ወያኔው ታጋይ ሞራልን እየገነባ ወያኔን ለማስወገድ የሚወስደውን መስዋእትነትና ጊዜ በእጅጉ ያሳጥረዋል::
ወያኔን ለማንበርከክ በሚደረገው ትግል ሚዲያ አጋዥነቱ ባያጠያይቅም ሚዲያ በራሱ ወያኔን ለመሰለ በአንድ ጎሳ የተደራጄ ሰራዊት የሚታገዝ ሀይል አንድ ስንዝር አያንፏቅቀውም:: ዋናው ቁልፉ ያለው ወያኔን በሚገባው ቁዋንቋ ማነጋገር ብቻ ነው:: ከሶሪያና ከሊቢያ ትግል የምንረዳው መራራ ሀቅ ይህንኑ ነው::
እንደነ ክቡር ብርሃኑ ነጋ ያሉትን አትናገሩ የሚለውንዳካሄድ በበኩሌ አልቀበለውም:: ከ እግዚአብሔር በስተቀር የሰው ልጅ አውቆም ሆነ ሳያውቅ ሊሳሳት ይችላል:: ሰው ሰው እንደመሆኑ መጠን እርማት ያስፈልገዋል:: ያንን ካላደረግንም ሰብዓዊነታችን ዝቅ ብሎ አቤት ባዮች አሽርጋጆች ሆንን ማለት ነው:: ትግሉ እኮ የሚካሄደው በህዝቡ አስተዋጽዖ ነው:: ህዝቡን አስተዋጽዖ አድርግ ካልን ለመጠየቅም ለመገሰጽም ለመታረምም ራሳችንን ማዘጋጄት አለብን:: የመሪዎች እስረኝ ልንሆን አንችልም:: መሪዎችን መገሰጽ ደግሞ ወያኔ ሊያስብል አይችልም:: በ እድሩም በማህበሩም መሪዎች ይጠየቃሉ ይገሰጻሉ ይለወጣሉ ምንም አዲስ ነገር የለም:: በተለይ ፖለቲከኞች በትውልድ ላይ ቁማር ሊጫወቱ ስለሚችሉ መጠየቅ ሲያንሳቸው ነው:: እውነት ለትግሉ የሚያስብ ዜጋ ከሆነ ይበልጡን መጠየቅና መተቸቱ ሊያስመሰግነውና ሊበረታታ ይገባል:: የወያኔ ስታይል አትተቹንማ እዚህ ቦታ የለውም::
እርግጥ ነው ወያኔ የተለያየ ማስክ እየለበሰ ትግሉን ለማደናቀፍ ተፍ ተፍ ይላል:: ይሁንና ምርትና ግርዱን በወንፊት መለየት እንጅ ሁሉንም ግርድ ነው ብሎ መደምደም ትግሉን የበለጠ ያሽመደምደዋል:: በሌላ አነጋገር የወያኔን የቤት ስራ ሳናውቀው እየሰራን ነው ማለት ነው:: ለድርጅት ታማኝነትና ፍቅር አስፈላጊ ነው ሊበረታታም ይገባል:: ነገር ግን የድርጅት ፍቅር ከሀገር ፍቅርና ከተጨባጩ እውነታ በላይ ከሆነ ፍቅር መሆኑ ቀርቶ ስካር ይሆናል:: የድርጅት ፍቅር እውነትን ለማግኜት ሊጋርደን አይገባም:: ድርጅት በእውነት እንጅ እውነትን በድርጅት ለመሳል መሞከር ከስርዓተ አመንክዮ ጋር ይጣረሳል:: የወያኔ ተከታዮች የማይታከም በሽታም ይኸው ነው:: እውነትን በድርጅታቸው ተክልና ወርድ ለክተው ለመስፋት: ድርጅታዊ እውነትን በሌላው ላይ ለመጫን ደፋ ቀና በማለታቸው ነው ወያኔያዊነትን አይኑን ላፈር ያልነው:: ይህ በሽታም ወያኔን እንታገላለን በሚሉ ድርጅቶች ብቅ ብቅ ማለቱ ነገሮችን የበለጠ ውስብስብና ተስፋ አስቆራጭ እያደረጋቸው ነው:: ተቃዋሚውም ከዚህ አይነት ወያኔያዊ አካሄድ ራሱን ካላጸዳ በወያኔ የተመዘዘው ጦርም እንደሚደርሰው መገንዘብ ያለበት ይመስላል:: የአቶ አንተነህ ጦማርም ይህን አካሄድን ሳይቃጠል በቅጠል ለማለት የተወሰደ ከሀገር ወዳድ እና በራሱ ከሚተማመን ዜጋ የሚጠበቅ እርምጃ ነው::
ውድ ነሂማም ምክንያታዊ በሆነ መነጽር እንደምትመለከተው ተስፋ አደርጋለሁ::
በራሳችን አለም የማይኖረውን ሁሉ ወያኔ ወያኔ ከማለት ይልቅ ስህተቱን ምክንያታዊና በመረጃ በተደገፈ ነገር ማሳመን በራሳቸው ከሚተማመኑ ሰዎች የሚጠበቅ ነው:: ወያኔ ለመሆኑ ማረጋገጫ የለንምና! በመነቀፋችን ቡራ ከረዩ ከማለት ይልቅ ቆም ብሎ ወደውስጥ ስህተትን ለመታዘብ መሞከር የጥንካሬ ምንጭ ይሆናል:: በአንድ ቤተሰብም የሃሳብ ልዩነት መኖሩን መገንዘብ አለብን:: ያልመሰለን እንደ ጠላት መፈረጅ የሚለው ዘይቤ ደግሞ የወያኔ የራሱ ቡኩር ልጅ ስለሆነ ከዚያ የተለየ ምክንያታዊ ተቃዋሚ ናፍቆናል::
ከአክብሮት ጋር
ዋቆ ዘአጋሮ
Ethiopian!ESAT belongs to Ginbot—–7………ECADForum belongs for the cause of Ethiopia.We are not worried about those who wish to bring freedom without sacrifices!We shall never give up Ethiopia for any power monger opportunists!
ፅሁፉን ከመጀመርያ እስከ መጨረሻ እና እንዲሁም አንዳንዶቹን አስተያየቶች (በተለይ የዋቆን) ካነበብኩኝ በኋላ, ወደ ጥንቱ መፈክሬ ለመመለስ ወሰንኩኝ:: ምንም እንኳን ፈቃድ ሳይጠይቀኝ, ወይንም ደግሞ ሰርቆኝ ወይንስ ቀምቶኝ ለመሆኑ ሳያስታውቀኝ የማሌሊቱ ORGAN-AIGA እየተጠቀመበት ያለ ቢሆንም, የራሴ የሆነውን መፈክሬን ለማንሳት ወሰንኩኝ:: እርሱም “UNITY IN DIVERSITY” የሚለው ነው:: ማለትም ለጠቅላላዋ ኢትዮጵያችን ያለኝን ፍቅር ለመግለጽ በማሰብ!! ከዚህም በማያያዝ አንድ ባልደረባችን ከጻፋቸው አረፍተ ነገሮች ትንሽ ቆንጸል አድርጌ ላስቀምጥላችሁ ወሰንኩኝ! አባባሉን ኮምፕዩተሩ ቢያንስ ወደ ከጀርመንኛ ወደ እንግሊዘኛ እንደሚተረጉምላችሁ ባለሙሉ ተስፋ በመሆን ነው::
“Aber in der Liebe zu unserer Heimat MIDRE-TSION-Äthiopien halte ich auch mit. Meine Heimat ÄTHIOPIEN: Von HAHAYLE bis nach TCHILA, von Yeha bis nach Tsion, von Damo bis nach Lalibela von Axum bis Gondar, von ADUA bis nach Metema, von Shire nach Harar, von Afar in den ganzen großen Graben bis nach Arba Minch, von Bizen nach Debre Libanos, von Bahir dar bis nach Bale-Jijiga, von Tana See bis nach Abaya-Chamo ist alles von Gott so schön gestaltet worden, wie sonst nur Italien von den Italiener in deren großartigen Kunstgestaltungen und in ihrer Baufähigkeit und Architektur. Die Schluchten von Mereb-Tekeze-Abay(Nil) und die himmlischen Berge von Adua – Alaje -Ras Dashin (das Dach Afrikas) bis nach Zquala und Bale Goba sind ebenso wunderbar.Deshalb doch das ewige Begehren der Italiener an Äthiopien und der Wunsch, so oder so nach Äthiopien kommen zu wollen, weil sie beides zusammen besitzen möchten: Kunst und die Schönheit der Natur. Sie dürfen ohne böse Absichten nach Äthiopien kommen. Friedlich sind sie uns willkommen in der schönen und alten biblischen Kultur.”