የታሪክ፡ ተጠያቂወች፡ አንሁን፤ የምግብ፡ ዋስትና፡ አለም፡ አቀፍ፡ ስብሰባ፡ ጠቃሚነቱ፡ ለኢትዮጵያዊያን፡ ነውን? ክፍል፡ አራት አክሎግ፡ ቢራራ (ዶር)

June 7th, 2012 ይመይሉ ይመይሉ ያትሙ ያትሙ
  1. ተውብል
    | #1

    ታሪክን ያጠፋ ምን ተጠያቂነት አለበት ?

  2. በለው!
    | #2

    ክቡር ዶ/ር አክሎግ ቢራራ ዛሬም እንደወትሮው መልካም ትምህርትን በበቂ ማስረጃ እና ትንታኔ አስተምረዋል እንግዲህ ጆሮአቸው ላይ ተቀምጠው ለማይሰሙ: አይኔን ግንባር ያድርገው ለሚሉ:የግል ጥቅማቸው ስለተሳካ እነሱ በልተው ጠግበው ድሃውን አግሳልን ብለው የሚያሰቃዩ, ሕዝብ እንዳይናገር አፍነው ተደስቻልሁ,ጠግቤአልሁ,ልጆቼ ጠግበው መድፋት ጀምረዋል ያለው የገዢ መደብ ተስማምቶኛል ብሎ ገበሬው አለቀሰ,እያሉ ሃያላን መንግስታት ፊት ተዋርደው ለሚያዋርዱን በጣሙን እናዝናለን:ሀገራችንን ጎብኝተው በትዝብት ብዙዎች ደፍረው ውሸትን ያስተባብላሉ አጋልጠዋልም::

    *ፕ/ት ሁሴን ኦባማም ቆመው በሽርደዳ ማንቆለጳጰፃቸው ሲያስቅ በሚቀጥሉት የስብሰባ ቀናት “ብዙ የመወያያ ነጥቦች አሉን በስፋትና በጥልቀት የምናየው የምግብ ዋስትና እንዳልፉት ጊዜያት ለአፍሪካ ይህንን እረዳን ስንል የሚምጣልንም ምላሽ ጥሩ ነገር ተሰርቷል ለውጥ ተገኝቷል የሚል ነው:በዓይን የሚታይ ነገር የለም አሁን ግን አሰራራችንን አጠናክረን በቂ የጽሑፍ ማስርጃ ሪፖረት ያስፈልገናል”ብለዋል እውነት ያደርጉት ይሆን??

    **ለእድገት ዴሞክራሲ አያስፈልግም !የሚሉት በቀን ሶስት ጊዜ ከበላህ ሌት ተቀን እድሜ ልክ ባሪያችን ነህ ማለታቸው ነው? ለአፍሪካ ከሚሰጥ ጠቅላላ ድራጎት ፳፭ ከመቶ የምትቦጭቅ ፹ ሚሊዮን የሕዝብ ብዛት ያላት ከጠቅላላ የሕዝብ ብዛቷ ፶ ከመቶ ዕድሜያቸው ከ፳ ዓመት በታቸ የሆኑ ናቸው። ሥራ አጡ ፵፭ ከመቶ ደርሷል፣ ሀገሪቱ በአምስት ዓመት (በተለጠጠው) (በተንበላጠጠው) የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ከመካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገሮች ጎን ትሰለፋለች ? ? ?

    ከዚህ በፊትም ወዳጃችን ክቡር ዶ/ር ፍቃዱ በቀለ በትጋት መክረዋል አስተምረዋል ስለመልካም የዜግነት ቁርጠኝነታችሁ ሀገር እና ሕዘባችሁን ለመታደግ እውቀታችሁን ይዛችሁ ከወገን ቆም በመሰለፋችሁ ታላቅ ምስጋናና አክበሮቴ ባላችሁበት ይድርሳችሁ በርቱ ህዘብ የማወቅ ዕድል ማግኘት አለበት!ኢትዮጵያ እጆቿን ዘርግታ ቅን አሳቢ ልጆቿን ትሰበስባለች።!!
    አሜን በለው !

  3. ነሂማ ወርጂ
    | #3

    የኢኮኖሚ እድገት የሚሉት የትቂት የወያኔ ካድሬዎችን ኪስ ነው. እንጂ ህዝቡማ በቀን አንዴ እይበላ እንደምናየው ነው. ብህዝብ ገንዘብ እንሱ ይበለጽጋሉ ህዝብ በርሃብ ይረግፋል .በያለንበት የነዚህን ህዳሞች ስም መያዝ አለብን መትፋታቸው አይቀርም. አንድም እርዳታ ሰጭ ተብዬ ነው በህዝብ ገንዘብ መሳርያ እየገዛ የህዝቡን መከራ እያረዘሙት ያለው እናም አሜሪካ እና እርዳታ ሰጭ ተብዬዎች ተጠያቂዎች ናቸው በተለይ ረርዳታ ሰጭዎች. ገንዘቡ የት እንድሚወል እያወቁ እና ሊትዮጲያ ህዝብ ውለታ ዋልን ሊሉ ነው???? እናም አቶ አክሎክ ጥሩ ብለዋል ይህን ሌባ ማጋለጥ አይታክቱ.

  4. ለጋሾች ከተጠያቂነት እንዳያመልጡ !!!
    | #4

    በመጀመሪያ ወንጀልን በመሪጃ በማቅረብዎ አመሰግናለሁ

    ቀጥሎም የውጮቹን መንግስታትና አበዳሪዎች ያሉትን ልጥቀስና ጥያቄ ላቅርብልዎት

    ‘…የውጭ፡ እርዳታ፡ ሙስናን፤ ስርቆትን፤ የሃብት፡ ሽሽትን፤ ኪራይ፡
    ሰብሳቢነትን፤ የሃብት፡ ክምችን (concentration of incomes and assets)፤ ጥገኝነትን፡ አጠንክሯል።…

    ለጋስ፡ የሆኑ፡ የውጭ፡ መንግስታትና፤ አበዳሪ፡ ድርጂቶችም፡ እድገት፡ አለ፡ ብለው፡ ሲናገሩ፡ ማስረጃውን፡ የሚያገኙት፡ ክህወሓት፡ ነው።…’

    ጥያቄዬ በሶስት እከፋላለሁ

    1. ወንጀልን ለሚሰራ ሆነ እንደሚሰራ እየታወቀ በገንዘብም ሆነ በማንኛውም መንገድ መርዳት በህግ አያስጠይቅም?

    በዓለም አቀፍ ደርጃ ሕጋዊ እርምጃ በነዚህ መንግስታት ላይ መውሰድ ይቻላል?
    ማንም ድርጅት ሆነ ግለሰብ በእርዳታ ስም ይሁን ብድር ስም የገንዘብና መሳሪያ ድጋፍ
    ወንጀል እንደሚሰራበት እያወቀ ለወንጀል ፈጻሚው ድጋፍ ካረገ በህግ መጠየቅ አይቻልምን?

    2. ለጋስ አገሮች ይሁኑ ድርጅታችው ወይም ግለሰብ በአንድ አካባቢ ሲንቀሳቀስ ለሕዝቡ በቃንቃው ጽሁፋዊ መረጃ መስጠት ግዴታ የለባቸውም አለባቸው?

    ከምረዳው ብዙዎቹ ለጋስ አገሮችና ርዳታ ድርጅቶቻቸው ስለ እንቅስቃሴያቸው ሆነ ያለባቸውን ግዴታቸው በተመለከተ በአገር ውስጥ ላለው ብዙሃኑ ሕዝብ ምንም ዓይነት መረጃዎች በቃንቃው በጽሁፍ አያቀርቡም ይህም ድርጊት በራሱ ሕዝቡን መብት የተጋፋ መሆኑን በህግ መጠየቅ አይቻልምን?

    3. ይህንን ህግ መጣስ በተመለክተ እሳትና መሰሎችም ይህን ቅስቀሳ የሚረዳ ፕሮግራም ማዘጋጀትና ማጋለጥ ስራ መስራት አይችሉምን

    በይበልጥ ለዚህ ወንጀል ተባባሪ የምንላቸውንና መቀመጫቸው ውጭ የሆኑትን ድርጅቶች ቃለ መጠየቅ መጋበዝና ይበልጥ ቅስቀሳ ማድረግ አይቻልምን?

    በይበልጥም አገር ውስጥ ያሉት ፓለቲካ ድርጅቶችና ግለሰቦች ቢተባበሩ የነዚህን ድርጅቶች ስራ ማጋለጥ አይቻልምን?

    የተማረውም ሕዝብ ሆነ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ለምን ይህን ድርጊት ላንድ ህዝብ ንቀት መሆኑን ተገንዝበው አይከራከሩም ሕዝቡም ይህን ጥያቄ እንዲያቀርብ አይቀሰቀስም?

    አመሰግናለሁ

  5. ለጋሾች ከተጠያቂነት እንዳያመልጡ !!!
    | #5

    ያልጠቀስኩት ነገር ቢኖር
    አንድ ችግር ካሳሳበንና ህልውናችንን ሲፈታተን በመረጃ ተደግፎ ውይይት ማድረጉ ተገቢነቱን ሁላችንም አንዘነጋም
    ቀጥሎም አቅምን ያገናዘበ መፍትሔ የሚሆን ተግባራዊ ምላሽ ካልሰጠን ተስፋ መቁረጥን ያመጣል
    ችግሩንም መላመድ ይመጣና ውስብስብ ይሆናል

    አመሰግናለሁ

አስተያየት መስጫው ተዘግቷል።