ትዝታ – ሀዲስ አለማየሁ ቅኝት – መስፍን ማሞ ተሰማ

June 18th, 2012 ይመይሉ ይመይሉ ያትሙ ያትሙ
  1. ለጋሾች ከተጠያቂነት እንዳያመልጡ !!!
    | #1

    በመጀመሪያ በመጀመሪያ አመሰግናለሁ
    ሆኖም መረጥ መረጥ አርገህ ብታቀርብው ይመረጥ ነበር እላለሁ በምስጋና ቢሱ ዓይኔ

    ሌላው አስተያየቴ

    ሀ/ መጽሀፉን እንድገና ቢያትሙ ያልከው ነገር እኔም በሙሉ እደግፋለሁ ፈልጌ ያጣሁት በመሆኔ
    ለ/ መጽሀፉን በውሰት አግኝቼ ለማንበብ ታድያለሁ ለብቻዬ ገርሞኝም አሳዝኖኝ የነበረው የጳጳሱ አብርሃም ነገር ነው
    1. ክህደትን በሳቸው ደረጃ ባለመሳቤ ነው ይህም የሃማኖት መሪ በመሆናቸው ነው
    2 በይበልጥም የተከበሩበት አገርና ሕዝብ ሲሰቃይ የጠላት ሹመት መቀበላቸው ግራ ነበር ያጋባኝ ሹመት ታማኝነት
    ምልክትም ነውና
    3. ሌላው የግል ወዳጃቸው አምኖ የሰጣቸውን አደራ በዛን ዘመን መካድ ለኔ አሳዝኖኝ ነበር

    ሐ/ ያልጠቀስክውና እኔን ያስደነቀው ነገር ሀዲስ አለማየሁ ስለ ዘመናዊ ጦር ያላቸውን የሰጡት አስተያየት ነው
    እኔ የተረዳሁበት መንፈሱን ነው የምገልጸው በትክክል ካላስታወስኩ አርመኝ
    የድሮ ጦር በተመለከት ሲያትቱ ታማኝነቱ ለክልሉ መሪ ነው በመሆኑም እድገቱም ሆነ ሹመቱ በአካባቢው ይወሰናል የዚህም ጥቅም ስራው በአካባቢው ይታወቃል

    እኔ ይህንን ያነሳሁበት ነገር ለምን ዘመናዊ ጦር እያላት በቀላሉ አገር ይበተናል የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ይረዳል በማለት ነው ለምሳሌ ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን ዩጎዝላቭያ ሱማሌንም መውሰድ ይቻላል
    ለላው የሚያስፈራኝም አሁን ባለንበት ዘመን ጣልቃ ገቢ የሆኑ ቅጥረኛ የሆኑ ወታደሮች እየበዙ ነው
    አንድ አገር የራሳን ዜጋ አሰልጥና ባሁኑ ጊዜ ለሪጂኑ ጸጥታ ወይም ለተለያየ ሚሽን በዓለም ዙሪያ እየሄዱ ለማንም የሚያገለግሉ ለአገራቸው ጉዳይ ባዕድ የሆኑ ወታደሮች የበዙበት ዘመን ነው ብዬ ሰለሚሰማኝ ነው

    ነጻነትና ነጻነት በአገር የሚለው ሐሳብ ጠፍቶአል መሰለኝ
    ግለሰብ ሆነናል
    የጋራ ክብር በእግር ካስ የሚታየው ያህል እንካን አያንገበግብም አያጣላም ልበል?

    መ. ጣሊያን አገር ገጠመኛቸውን በተመለክተ

    የጣሊያን ባለስልጣን ራስ እምሩን እስር ቤታቸው መጥቶ ሊያናግር ሲመጣ ህዲስ አለማየሁ ወንበር ሊስጡ ሞክሩ
    ራስ እምሩ አንተ ለሱ ወንበር ለምን ትሰጣለህ እሱ ከፈለገ የራሱን ወንበር ማዘጋጀት ይችላል ማለታቸው
    መብትንም ክብርንም በእስር ሁነው አልተውም

    ያለንበትና መጪው ዓለም ጦርነት አገራዊ ሳይሆን ዘር ላይ የተመሪኮዘና ሙስናን መዋጋት ይመስለኛል
    ሃይማኖትና አገር የሚባሉ ነገሮችን በዘዼ በግለሰብ መብት ተተክቶ ትርጉም በሚሰጥ ሁኔታ መታገል እንዲጠፋ ተደርጋል
    ሰለብሪቲ ባህሉ የታዳጊ አገር መሪዎችንና ሃይማኖት መሪዎችን ሳይወከሉ ተክተው መናገር መፈትፈት ጀምረዋል
    ስለዚህም ግሪኩንና ጣሊያኑን መሪ የፋይናንስ ድርጅቶች ከስልጣን ሲያነሱ አይተናልና የኛም እጣ ከዚህ ውጭ አልሆነም

  2. ደርብ ቀጀላ
    | #2

    ክቡር ሐዲስ ዓለማየሁን በሚገባ ኣዉቃቸዋለሁ:: እንዴት?
    የዘመዳችን ኣያየ (ራስ ኣምሩ ሐይለ ስላሴ) ዋና ባልንጀራ ስለነበሩ ዘወትር ሐሙስ ኣለት
    ኣባኮራን ስፈር ባለዉ መኖሪያ ቤት ሲመጡ ኣገኛቸዉ ነበር::
    ኣያየና ሐዲስ ስለፋሽስቱ ወረራ ዘመን ሲያወሩልን በከፍተኛ ተመስጦ ሰምቻለሁ:: በዚያን ወቅት
    የቀ.ሐይለ ስላሴ ዩንበርስቲ የሳይንስ የኬሚስትሪና ፊዚክስ ተማሪ ስለነበርኩ ኣልረሳሁትም::
    ሁለቱም ሲተርኩ በጥንቃቄ እንስማ ነበር::
    የማይረሳኝ ከሁሉም በላይ ስለሳይንስ ትምህርቴ ዘወትር የሚጠይቁኛ የሚሰጡኝን ማበረታት ከቶ
    አልዘነጋዉም::
    ሌላዉ በሕይወቴ የማልዘነጋዉ ሀዲስ በ1966 በአብዮት ተብዬዉ ማመሳቀል ወቅት ኢትዮጵያ ምን ኣይነት አስተዳደር ያስፍልጋታል በሚል ራእስ ትንሽ መጽሐፍ ጽፈዉ ነበር::
    ከአዉሮፓና አሜሪካ ሮጠዉ የመጡት አብዮተኞች ሳይንሳዊ ሶሻሊዝም ብለዉ በአዲስ ዘመን ጋዚጣ
    ላይ ዉሃ ቀጠነ: ወተት ጥቁር ሆነ የሚል ከንቱ ከንቱ ትችት ኣቀረቡባቸው::
    የፈሩት ይደርሳል: የጠሉት ይወርሳል እንዲሉ አረመነዉ ደርግ ስልጣን ያዘ::
    ቀጥሎም ኣብዮተኞች ርስ በርስ ጦርነት ኣድርገዉ ወጣቱን ለቀይና ነጭ ሽብር ዳረጉት::
    ደርጉም አገር ኣዋይ ሁሉን ኣዉድሞ: ወጣቱን ጨፍጭፎ: ለነወያኔ ሻእቢያ ጥርጊያ መንገዱን ኣዘጋጅቶ ፈረጠጠ:: በዘመነ ወያኔ በኣገራችን ኣፓርታይድ የጎሳ ፖለቲካ ሰፈነ::
    ኢትዩጵያ ተሸጠች::
    ልጆቹዋ ሰደተኞችና ተመጽዋች ለማኝ ሆኑ::
    እነሃዲስና አያየ ይህን ጉድ ቢያዩ ምን ይሉ?

    ድርብ ቀጀለ
    ጆሌ ወበራ

  3. ለጋሾች ከተጠያቂነት እንዳያመልጡ !!!
    | #3

    ለውይይት መነሻ እንዲሆን ጽፈሃልና ውይይትም ተግባራዊ ምላሽን መጠቆም ካልቻለ ውይይት ሳይቃጭ ይቀራል
    ስለዚህም ሀሳቤን ላስፍር

    አገር ስልጣን ሃብትና ሹመት በተመለከተ ነው

    አገርና ሃይማኖት መከበር መታገል ቀርቶ ለግለሰብ መብት ብቻ የሚል አስተሳሰብ ስር ስለሰደደ ይህንን ጉዳይ መፍታት ትልቁ ችግር ነው
    ለምሳሌ በዛሬው ዓለም የአንድ አገር ዜጋ ሌላ አገር ዜግነት ለመውሰድ ፈጽሞ ለራሱ ወገንና አገር ባእድ ሆኖ መስራት በሰፊው ይታያል ይህን ወደ ጥቅም ለማምጣት ይቻላል የሚሉ ወገኖች አሉ በእነ ዓይን አይቻልም ነው

    አገር መሪነት ስልጣን ሰጪና ነሺው አገሩ ሰው መሆኑ ቀርቶአል በአፍሪካ ዓረብና እስያ ያሉ መሪዎች ስልጣናቸው ምንጭ የውጭ አገሮች ናቸው ለዚህም ብዙሃን መገናኛና ትምህርት ቤቶች ትልቁን ስነ ልቦና ሰለባ በማድረግ አስተዋጽኦ አድርገዋል
    ይህ ሳይሆን ሲቀር መሪዎቹን በውሸት ክስና ውስጥ ብጥብጥ በማንሳት ይጥሉዋቸል

    ለምሳሌ ግብጹን ሳዑዲውን የፓኪስታንዋን መሪዎች መመልከት ይቻላል

    ሹመትና ሃብቱ ከመሪዎቹ ጋር ተያይዞ የሚመጣ ነው

    በአገራችንም ብንመለከት ዊንገት ት/ቤት አሜሪካና ሊሴ ገብረ ማርያም ት/ቤቶች የመሳሰሉ የባለስልጣን መመልመያ ባህል መከለሻ ናቸው

    ከነጭራሹ ሊሲ ገ/ማርያም በፈረንሳይ ሕግ እንዲተዳደር ኮንትራት ተሰጥቶታል

    ይህንን ለመለወጥ ት/ቤቶችም ሆኑ ትምህርት በአገር ዜጋ ብቻ በአገር በጀት መሆን አለበት እላለሁ
    ይህ ካልሆነ
    ለምሳሌ ጭቁን ጭቁንን አይወጋም ብሎ የሶማሊያንን ወረራ መክላከል የለብንም የሚል ዜጋ ይፈጠራል

  4. ዜግነት ሃላፊነትና ትምህርት የተያያዙ ናቸው
    | #4

    ለውይይት መነሻ እንዲሆን ጽፈሃልና ውይይትም ተግባራዊ ምላሽን መጠቆም ካልቻለ ውይይት ሳይቃጭ ይቀራል
    ስለዚህም ሀሳቤን ላስፍር

    አገር ስልጣን ሃብትና ሹመት -ስልጣኔ በተመለከተ ነው

    1. አገርና ሃይማኖት መከበር መታገል ቀርቶ ለግለሰብ መብት ብቻ የሚል አስተሳሰብ ስር ስለሰደደ ይህንን ጉዳይ መፍታት ትልቁ ችግር ነው
    ለምሳሌ በዛሬው ዓለም የአንድ አገር ዜጋ ሌላ አገር ዜግነት በመውሰድ ለራሱ ወገንና አገር ፈጽሞ ባእድ ሆኖ መስራት በሰፊው ይታያል ይህን ወደ አገር ጥቅም ለማምጣት ይቻላል የሚሉ ወገኖች አሉ በእነ ዓይን ግን አይቻልም ነው
    ስለዚህ ስደት የሚቀርበትን ሁኔታ መፈለግ ግድ ይላል

    2. ስልጣን ሰጪና ነሺው አገሩ ሰው መሆኑ ቀርቶአል
    በአፍሪካ ዓረብና እስያ ያሉ መሪዎች ስልጣናቸው ምንጭ የውጭ አገሮች ናቸው
    ለዚህም ብዙሃን መገናኛና ትምህርት ቤቶች ትልቁን ስነ ልቦና ሰለባ በማድረግ አስተዋጽኦ አድርገዋል
    አንድ አገር መሪ ስልጣኑ መሰረት የአገሩ ሲሆን ፍላጎታቸው ያልተሳካላቸው ውጭ አገሮች መሪዎቹን በውሸት ክስና የውስጥ ብጥብጥ በማንሳት ይጥሉዋቸል

    ለምሳሌ ግብጽ ፓኪስታን ሳዑዲ ምሪዎችን መመልከት ይበቃል
    በተቃራኒው የሊቢያ መሪ ብንወስድ በአገሩ የሕዝቡን ኑሮ ብንመለከት ክማንኛውም የሰሜን አፍሪካ የተሻለ ነው ይባላል ሁኖም ስላልተፈለግ እንዴት ከስልጣን እንደወረድ መመልከት ይበቃል

    3. ሀብትና ሹመቱም ከመሪው ጋር ተያይዞ አብሮ ይመጣል
    ሙስናውም አብሮ ይመጣል

    መፍትሄው በእኔ እይታ ስልጣኔ የሚለውን ሃሳብ አልገባንምና እንደገና መማር አለብን
    ስልጣኔ በት/ቤት በኩል ይሰጣል ብንልም ትምህርቱንም በጀቱንም ሃላፊነት ለውጭ አገሮች አሳልፈን ሰጥተናል

    ትምህርት ቤቶች ሆኑ ትምህርቱ ካሪኩለም በአገር በጀትና በአገሩ አስተማሪዎች መመራት አለበት
    ዛሬ የምናየው ሊሲ ገ/ማርያም ት/ቤት በፈረንሳይ ሕግ ይተዳደር ተብሎ ኮንትራት ተሰጥቶታል
    ከ80% የሚበልጠው የት/ቤቱ ተማሪ ኢትዮጵያዊ ዜጋ መሆኑ እየታወቀ በፈረንሳይ ህግ መተዳደሩ ለተማሪው የበታችነትን ማስተማር ነው እላለሁ

    ጉዳቱን ለማስረዳት አንድ ምሳሌ እጥቅሳለሁ
    በ70ዎቹ የሶማሊያ ጦር ኢትዮጵያን ሲወር ጭቁን ጭቁንን አይወጋም ብለው ለሶማሊያ የሚያግዝ ዜጋና ፖሊካል ፓርቲ መኖሩ
    አገር የሚለው ግንዛቤ ተማርኩ ከሚሉት ዜጎች አዕምሮ ልጠፋ እንደቻል ያሳያል

    ስለዚህም ትምህርት የጋራ ዜግነት ግዳጅ እንዲወጣ ካላካተተ ዋጋ የብለን ነው
    እትብት መቀመጫቸው ኢትዮጵያ ብቻ መሆኑ አይበቃም

    ትምህርቱን በወሳኝነት ያየሁበት ምክንያት የውጩን የበላይነት እንደጡጦ ተሎግሞ ስለሚግተን ነው

    አመሰግናለሁ

  5. የበላይነሽ?
    | #5

    ለውይይት መነሻ እንዲሆን ጽፈሃልና ውይይትም ተግባራዊ ምላሽን መጠቆም ካልቻለ ውይይት ሳይቃጭ ይቀራል
    ስለዚህም ሀሳቤን ላስፍር

    አገር ስልጣን ሃብትና ሹመት በተመለከተ

    አገርና ሃይማኖት መከበር መታገል ቀርቶ ለግለሰብ መብት ብቻ የሚል አስተሳሰብ ስር ስለሰደደ ይህንን ጉዳይ መፍታት ትልቁ ችግር ነው
    ለምሳሌ በዛሬው ዓለም የአንድ አገር ዜጋ ሌላ አገር ዜግነት ለመውሰድ ፈጽሞ ለራሱ ወገንና አገር ባእድ ሆኖ መስራት በሰፊው ይታያል ይህን ወደ ጥቅም ለማምጣት ይቻላል የሚሉ ወገኖች አሉ በእነ ዓይን አይቻልም ነው

    ስልጣን ሰጪና ነሺው አገሩ ሰው መሆኑ ቀርቶአል በአፍሪካ ዓረብና እስያ ያሉ መሪዎች ስልጣናቸው ምንጭ የውጭ አገሮች ናቸው ለዚህም ብዙሃን መገናኛና ትምህርት ቤቶች ትልቁን ስነ ልቦና ሰለባ በማድረግ አስተዋጽኦ አድርገዋል
    ይህ ሳይሆን ሲቀር መሪዎቹን በውሸት ክስና ውስጥ ብጥብጥ በማንሳት ይጥሉዋቸል

  6. genanaw
    | #6

    ደርብ ቀጀላ

    በጣም ጥሩ ዓስተያየት

አስተያየት መስጫው ተዘግቷል።