“ሰው ምን ይህል መሬት ይፈልጋል” ? በበላይነህ አባተ

August 19th, 2012 ይመይሉ ይመይሉ ያትሙ ያትሙ
  1. መረተውርቅ
    | #1

    በርግጥ ጥሩ ምክር ነው ለሚገባው ሰው የሰው ልጅ በገንዘብ ፍቅርና እራሱን ከሌሎች ከፍ አርጎ ለመታየት የማያደርገው ነገር የለም ለገዛ ወንድሙም ደንታ ያጣል!ግን ሃብታም ለመሆን ግፍና በደል ሰርቶ በሃጢአት ከመነከር መልካም ስምና ያለኝ ይበቃኛል ብሎ እግዚአብሔርን ሳያሳዝኑ ሰውን ሳይበድሉ መኖር ትልቅ ጸጋ ነው…ክፎዋች በደም ያከማቹትን ሳይበሉት ጥለው ይሄዳሉ ግን አይማሩም!ሌባ ይሰርቃል እንጂ አይበላውም ተይዞ እስር ቤት ሲማቅቅ ይኖራል! ግን ሁልግዜም ሌባ አይጠፋም ለምን አይማሩም!!ግፈኛው መለስም ለመዘርዝር የሚከብድ በደል በሰውና በሃገር ላይ ፈጸመ ሞተ ብለው ለመናገር ከበዳቸው ለምን ሁሉም የጥፋት ሰዎች በመሆናቸው ሞትን ያህል እዳ ተሸክመው ነግ በኔ እዚህ ላይ ይብቃን አላሉም.. የክፋቆች መንገድና ሃሳብ አንድ አይነት ነው ያሳዝናል አጥፍተን እንጥፋ! ሁሉን የሚቻለው አምላክ ግን እስከመጨረሻው አይታገስም ክፍዎችን ያጠፋቸዋል! ድል ለኢትዮጲያና ለሕዥቦችዋ ይሁን!

  2. Anonymous
    | #2

    ዝተጀመረ ልምዓት ብሓባር ኮይንና ዕላምኡ ክነሳኽዖ ኢነ::ዘለአለማዊ ዝኽሪ ንኩሎም ሰማእታትና!!

  3. ትግስት
    | #3

    የመለሰ ሞት ብቻውን በቂ ትምህርት ነው የኢትዮፕያ ህዝብ አሳዘነን ምክንያቱም በመለስ መሞት ከፍተና ሃዘን ተሰምቶአቸው ከቦሌ ጀምሮ አባቱ እንዳሞተበት እንባ እየተራጬ መኪናውን ሲከተሉ አሳዘኑኝ የኢትዮጵያ ሰው ሚስኪን ነው ያ ሁሉ ግፍና በደል የደረሰበት አይምስልም ስለዚህ እባካትሁ አምባገነኖት በዚህ ይብቃችሁ..

  4. በላይነሽ
    | #4

    እጅግ ግሩም ድንቅ ጹህፍ ነው::በላይነህ መጽሃፉን አነበዋለሁ::አንተም ጥሩ አድርገህ ነው ያቀረበከው::በጣም ጎበዝ አንባቢ መሆንህን ነው የተረዳሁት በርታ::በአንባቢነትህ ምሳሌ የምትሆን ስለሆነ አደንቅህ አለሁ::

  5. ፈቃዱ
    | #5

    እዚህ ድህረ-ገጽ የምትገቡ የወንድም በላይነህ አባተን ግሩምና ትምህርት አዘል ጽሁፍ እንዳነበባችሁ ተስፋ አደርጋለሁ። በዛሬው የግሎባል ካፒታሊዝም ዘመን ፈቅር እንኳ ሳይቀር ሁሉ ነገር በገንዘብ በሚለካበት ዓለም ውስጥ እንደዚህ ዐይነቱ ጽሁፍ በሰፊው መነበብና መጠናት ያለበት ነው። ምንም አንኳ የሰው ልጅ አርቆ የማሰብ ኃይል ቢኖረውም አብዛኛውን ጊዜ እሱን ሳይሆን የሚጠቀምበት ቶሎ ቶሎ ወደ ላይ የሚያወጣውንና ግን ደግሞ ቶሎ የሚያፈርጠውን ነው። ይህ ዐይነቱ አልጠግብ ባይነት የሰው ልጅ ስልጣኔ የሚባለው ዓለም ውሰጥ ተወርውሮ ከገባ ወዲህ እየባሰበት የመጣ ነው። እንደዚህ ዐይነቱን ከዕድገት ጋር የተያያዘ የሞራልና የስነ-ምግባር መበላሸት በጥንቱ የግሪክ ስልጣኔ የተያና ፕላቶም ሆነ አርስቲቶለስ ሲያስጠነቅቁ ነበር። ማንኛውም የሰው ልጅ ልኩን ማወቅ አለበት። የማቴርያልና የመንፈሰን ሁኔታ ሚዛናዊ በሆነ መንገድ መጠበቅ አለበት። እንደሚባለው የሰው ልጅ በዳቦ ብቻ አይኖርም። ፍቅርና ልዩ ልዩ መንፈስን የሚያድሱ፣ የማሰብ አድማሱን የሚያሰፉለትና በርግጥም ሰው መሆኑን የሚያረጋግጡለትን ነገሮች ማግኘት አለበት። በዚህ መልክ ብቻ በአንድ ህብረተሰብ ውስጥ ሰላም ይሰፍናል፤ መተሳሰብ ይኖራል። አንድ ህብረተሰብ ካለብዙ ግጭት ከአንድ ትውልድ ወደ ሌላው በቀላሉ ይሸጋገራል። እንደምናየው ዛሬ በዓለም አቀፍ ደረጃ በብዙ አገሮች የሚካሄደው ጦርነት ስልጣንና ገንዘብ ከመፈለግ የተነሳ እንጂ እውነተኛ ስልጣኔ በመሻት አይደለም። ወደኛ አገርም ስንመጣ በተለይም ባለፉት 21 ዐመታት የተካሄደውን የኢኮኖሚ ፖሊሲ ስንመለከት እኩልነትን ሳይሆን ጥቂቶችን የጠቀመና ያደለበ፣ እንዲሁም ደግሞ የሚሆኑትን ያሳጣ ነው። ሰፋ ያለ ምሁራዊና ትችታዊ ትምህርት በሌለበት እንደኛ ባለው አገር ውስጥ አገርን የሚያሸጥና ህብረተሰብን የሚያስንቅ ተግባር የመስፋፋት ኃይሉ ከፍ ያለ ነው። ስለዚህም ነው ዛሬ ከፍተኛ መካካድ የተስፋፋው። ይህንን ዐይነቱን ለስልጣኔና ለሰላም ጠንቅ የሆነውን የስግብግብነት ባህርይ በከፍተኛ ምሁራዊ ኃይል፣ በተለይም በኪነት፣ በካባሬትና በሊትሬቸር እንዲሁም በስዕል መዋጋት አለብን። በተረፈ አቶ በላይነህ የቶልስቶይን ግሩም ጽሁፍ ተርጉመህ በጣፈጠ መልክ ማቅረብህ የሚያስመሰግንህ ነው።በርታ !
    ፈቃዱ

  6. Yeleka
    | #6

    I dont think this people will learn from their mistake. They are very proud of about their past.They will continue their evil doing. Sooner or later they will pay the price lik their devil frind. God is great.

  7. Yeleka
    | #7

    You did good Adugida we dont need to see their arrogance and west our time by reading their trash. Weyane or Sabiya where they like it or not they will disapper for ever. Egzeabher Ethiopiana Legohuan yetebek

  8. ፈቃዱ
    | #8

    የአቶ በላይነህ አባተ ጽህፍ እንዲያው ዝም ብሎ የሚታለፍ ጉዳይ አይደለም። ህብረተሰብአዊ፣ ፍልስፍናዊና እንዲሁም ሳይኮሎጂያዊ ንጥረ-ነገሮችን የሚያሳይ ነው። አንድ ህብረተሰብ ከአንድ ዘመን ወደ ሌላ በሚሸጋገርበት ወቅት የሚያመጣውን የአስተሳሰብ ለውጥ የሚያሳይ ነው። የአስተሳሰብ ለውጥ በክፉም ሆነ በደግ ሊገለጽ የሚችለው በህብረተሰብ ውስጥ ከውጭ በሚመጣ ወይም ከውስጥ ከረዢም ጊዜ ክርክር በኋላ በሚፈልቅ ዕውቀት ነው። ጥራዝ ነጠቅ ከሆነ የአንዳንድ ግለሰቦችን ባህርይ የሚያበላሽ፣ ስግብግብነታቸውን የሚያጠናክርና ህብረተሰብአዊ ኃላፊነት እንዳይኖር የሚያደርግ ነው። ለኔ ብቻ የሚለው አስተሳሰብ በመጠንከር ህጋዊ በሆነ መልክ የማይቻል ከሆነ በቅጥፈት ሀብት ለማጋፈፍ ብዙ ቲያትር የሚሰራበት ነው። ስለዚህም የቶልስቶይ ጽሁፍ ራሺያ ከፊዩዳሊዝም ስርዓት ቀስ በቀስ በመላቀቅ በሞኔተሪ በሚገለጽ ካፒታሊዝም ወቅት በደረሰ አዲስ የህብረተስብ ክስተት ላይ የተመረኮዘ ነው። ዛሬ ይህ ዐይነቱ አብዛኛውን ህዝብ መገፍተርና ማድኸየት በየቦታው እንደፈሊጥ እየተወሰደ መጥቷል። ኢንቬሰተርስ የሚባሉ ከመንግስታት ባለስልጣናት ጋር በመቆላለፍ ሺህ በሺህ የሚጠጉ የዋህ ህዝቦችን ከትውልድ ትውልድ ከተላለፈ መኖሪያቸው በማፈናቀል መጠጊያ የሚያሳጣ ዘዴ ነው። በየአገሮች ዘላቂነት የሚኖረው የኢኮኖሚ ግንባታ ከማካሄድ ይልቅ ለጥቂቶች ብቻ እየተባለ ብዙ ህዝብ ከአገሩ የሚፈናቀልበት ሁኔታ እየተፈጠረ ነው። እያንዳንዱ ህዝብ የየራሱ የጥሬ ሀብት ተቆጣጣሪ የማይሆንበት ሁኔታ ተፈጥሯል። ከዚህ ስነሳ የአቶ በላይነህ ጽሁፍ በአንድ ትችት ብቻ የሚታለፍ አይደለም። የኛንም አገር ሁኔታ በቀጥታ ሰለሚመለከት ለዕውነተኛ ነፃነት እንታገላለን የምትሉ ይህ ዐይነቱን የበሰለ አቀራረብ በጥሞና አጥንቶ ማስፋፋት የሚገባ ይመስለኛል።

    ፈቃዱ

አስተያየት መስጫው ተዘግቷል።