ማህደር

ማህደር ለ June, 2009

እረፍት አድርግ አሁን – ጌታቸው አበራ ለማይክል ጃክሰን

June 30th, 2009
Comments Off

አማራ የቀነሰው ህዝቡ ወይስ ቁጥሩ? – እስከ ነፃነት

June 29th, 2009

በቅርቡ የስታትስቲክስ ጽ/ቤት በአማራ ክልል የተደረገው ቆጠራ ትክክል ነበር መድገም አያስፈልግም ብሎ በተወካዮች ምክር ቤት ማጽደቁን ሰምተናል: በዚህም ቆጠራ የአማራ ክልል ህዝብ ከተተነበየው ወደ 2.4 ሚሊየን አካባቢ ዝቅ ብሎ ታይቷል: የስታትስቲክስ ጽ/ቤት ኃላፊዋ ሳሚያ ዘካሪያ የህዝቡ ቁጥር ዝቅ ያለበትን ምክንያት እንደሚከተለው መዘርዘራቸውም ይታወሳል: Read more…

ዜና

መልዕክተ ኦባንግ – ስለሺ ዘእንግልጣር

June 29th, 2009

“የምንታገለው ለመንደር ወይስ ለሐገር? መታገል ያለብን ለሐገር አነድነት ነው፣ ሐገር ከሌለች መንደር አይኖርምና።”

አቶ ኦባንግ ሜቶ ‘የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የትብብር ንቅናቄ’ መስራች ከተናገሩት ተተርጉሞ የተወሰደ Read more…

ዜና

የአንድነት ፓርቲ እንቅስቃሴዎችን በሰፊዉ እያደረገ እንደሆነ ተዘገበ

June 27th, 2009

አቡጊዳ – ሰኔ 20 2001

የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ፣ ሕዝቡ በወ/ት ብርቱካን ሚድቅሳ ላይ ከስድስት ወራት በላይ እያየደረገ ያለዉን የጭካኔ ግፍ አስቦ በየአብያተክርስቲያናቱ፣ መስኪዶች እንዲሁም በቤት፣ እሁድ ሰኔ 21 ቀን 2001 ሻማ በማብራት ጸሎት እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።

ጥሪዉ አገር ዉስጥ በሚታተሙ ጋዜጦችና በየክልሉ ባሉ የአንድነት መረብ አማካኝነት በሰፊዉ ለሕዝብ የተነገረ ሲሆን፣ በይዘቱ የፓርቲዉ አባላትን ከማሳተፍ ያለፈ ሰፊዉን ሕዝብ የጨመረ እንቅስቃሴ በመሆኑ በብዙዎች ዘንድ እንደ ትልቅ እርምጃ ተደርጎ እየተወሰደ ነዉ። ሕዝቡ በራሱ እንዲተማመን፣ ባለዉ አቅሙ ሁሉ እንዲንቀሳቀስ ካልተደረገ አንዳች ዉጤት ማምጣት እንደማይቻል የነገሩን አንድ የፖለቲካ ተንታኝ የአንድነት ፓርቲ ተከታታይ ሕዝብን የሚያሳትፉ እርምጃዎች በቀጣይነት መወሰድ እንዳለበት ገለጸዉልናል። Read more…

ዜና

በቃ፡ በቃን እንበል – ስለሺ ዘእንግልጣር

June 25th, 2009
Comments Off

እስከመቼ በግዞት፣ በግፍ ወከባ እስራት፣
በመባረር ስቃይ ማየት፣ ተሰዶ ከሐገር መውጣት። Read more…

Poem

ሁሉ ነገር በእጃችን ነዉ – በግርማ ካሣ

June 24th, 2009

ሰኔ 17 ቀን 2001

ኢትዮጵያን በጽጌረዳ አበባ እመስላታለሁ። ጽጌሬዳ አበባ በጣም ተወዳጅ የሆነች አበባ ናት። ብዙ ጊዜ በማስቀመጫ ዉስጥ ተደርጋ የሚመጡ እንግዶች እንዲያይዋት በሚታይ ቦታ ትቀመጣለች። የክብር የፍቅርና የዉበት ምልክት ናት። ኢትዮጵያ አገራችንም በነጻነቷና በአንድነቷ ታፍራና ተክብራ የኖረች፣ ከተለያዩ ብሄረሰቦች የተወጣጡ ልጆቿ ዉበቷ የሆኑላት፣ ለኢትዮጵያዉያን ብቻ ሳይሆን ለጥቁር ህዝብ ሁሉ ኩራት የሆነች አገር ናት። Read more…

ዜና

የሌባ ተረት – ብርዞ ፍራንክፈርት

June 22nd, 2009
Comments Off

የ አቦይ ስብሃት ግብና አባባል
የሚያቅለሸልሽ ጥሬ ግንፍልፍል Read more…

Poem

በቃኝ – ብርዞ (ፍራንክፈርት)

June 21st, 2009

በቃኝ አኔ በቃኝ አዎ በቃኝ በቃኝ
በደል ግፍ ስሰማ አኔን መሰል ስቃኝ
አልንበረከክም አጄንም አልሰቅልም
ህሊና አስገድሎ ሆድ ማዳን አይቀልም Read more…

Poem

እሽሩሩ – አስፋወሰን ዓለምሰገድ

June 21st, 2009
Comments Off

እሽሩሩ
እሽሩሩ
እሽርሩ፥ማሙዬ
ልንከባከብህ፥እሽሩሩ ብዬ
አባት ሆኛለሁ፥በተራዬ። Read more…

Poem

የደደቢቱ ፕሮፌሰር ተምኔታዊ ካፒታሊዝም – ደቻሳ ነኝ

June 21st, 2009

ማነው እሱ ወያኔዎች አፋቸውን ሲከፍቱ ባዶ አንጎላቸው ይታያል ያለው? አዎ ታየ እንጂ የታየው ግን ደደብነት ብቻ ሳይሆን እርቃኑን የቆመ ከርካሳ እብሪት ነው። ማሌሊት ማጭድ መዶሻዋን አስቀምጣ ሱቅ በደረቴ ሆነችና ስለካፒታሊዝም ትሰብከን ገባች። የወያኔ ‘ጎድ ፋዘር’ በመባል የሚታወቁት አቦይ ስብሀት ኮሙኒዝምም ይሁን ካፒታሊዝም ያለኛ አያምርበትም ብለው ነገር ሊተነትኑ ምድረ አሜሪካ ተገኙ። እኔ ግን ራሴን በርሳቸው ቦታ አድርጌ የነገዪቱን ኢትዮጵያ ተመለከትኳት:: Read more…

ዜና