ማህደር
ስም ልቀይርልህ – ማናለህ ከአሳረኛዉ ሀገር
ወያኔ እንበልተው! – (ከእስከ ነጻነት)
የወያኔ አባላትን ሁሉ በአንድ ቅርጫት ውስጥ መክተትና በአንድ አይን መመልከት፣ በአንድ ሚዛን መለካት ስህተት ነው እላለሁ: ወያኔን በባህሪያቱ መከፋፈልና በብልት ከፋፍሎ መመልከት ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አለው: Read more…
በቃሊቲ እሥር ቤት ሰሞኑን የተከሰተዉን አሳዝኝ ሁኔታ በተመለከተ – ግርማ ካሳ
muziky68@yahoo.com
ሰኔ 9 ቀን 2001
ቶርቸር (ሰቆቃ) ከአለም እንዲጠፋ የሚታገል የአለም አቀፍ የጸረ-ቶርቸርና የተጎጂዎች ደጋፊ ድርጅት፣ የአይምሮን ቶርቸር ሲተነትን፣ ረዘም ላለ ጊዜ በጨለማ ቤት ዉስጥ ማስቀመጥን፣ እንቅልፍ ማሳጣትን፣ መድፈርንና የመሳሰሉትን ከቶርቸር ዉስጥ ያስገባቸዋል። በእንደዚህ አይነት የአይምሮ ቶርቸር የሚያልፉ ሰዎች እራሳቸዉን እንዲጠሉ የሚያደርግና የሚቆይ ከፍተኛ የአይምሮ በሽታን እንደሚያመጣ ይናገራሉ።
የለንደን ዪኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ከቤልግሬድ የሕክምና ኮለጅ ጋር በመተባበር 279 የቀድሞ እሥረኞችን በማነጋገር፣ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ መረጃዎችን ሰብስበዋል። በሰበሰቡትም መረጃ መሰረት የደረሱበት ድምዳሜ የአይምሮ ቶርቸር ከአካላዊ ቶርቸር በምንም እንደማይለይ የሚገልጽ ነበር። የአይምሮ ቶርቸርን እንደ አካላዊ ቶርቸር የሚያግድ አለማቀፋዊ ሕግ መዉጣት እንዳለበትም አሳስበዋል። Read more…
ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ለስድስት ወራት ከተቀመጡበት የጨለማ ቤት ወጡ ! – ልዩ ዘገባ ¬አወደ ኢትዮጵያ
ሰኔ 8 ቀን 2001
ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር፣ ከአንድ መቶ ስድሳ አመስት ቀናት በላይ፣ ሁለት ሜትር በሁለት ሜትር በምትሆን የጨለማ ክፍል ዉስጥ እንዲታሰሩ መደረጉና በአንድ ነፍሰ ገዳይ እንኳን ያልደረሰ ግፍ በወያኔ¬ኢሕአዴግ አገዛዝ እንደደረሰባቸዉ በሰፊዉ የተዘገበ ጉዳይ ነዉ። Read more…
ለማያዉቁሽ ታጠኚ – አባ በዝብዝ ዘካሊፎርኒያ!
ጎይታይ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከወያኔና ከተለጣፊ ድርጅቶች ሰራዊቶች ጋር የሀገራችን መናገሻ ከተማ ከሆነችዉ ሀዲሽ እንባባ ሲገቡ ያስጎሰሙት ነጋሪት፣ ያስመቱት ከበሮና ያስደለቁት “አያ በየነ” ዘፈን ትዝ ይለኛል። Read more…
“የግልገል ግቤ-3 እና የላሟ ታሪክ!” – ኩችዬ – ጁን
“ላም እሳት ወለደችና እንዳትልሰው እሳት እንዳትተው ልጇ ሆነ!”
ይህ አባባል ግለሰቦችም ማሕበረሰቦችም በኑሮ ሂደት ውስጥ አስጨናቂ ምርጫ እንዲያደርጉ የሚገደዱባቸው ሁኔታዎች መኖራቸውን የሚያመለክት ነው። እነዚህ ሁኔታዎች ብንዘጋቸው የማይዘጉ፤ መልስ እስካላገኙ ድረስ ከፊታችን ዞር የማይሉ ችኰ ነገሮች ናቸው። 3ኛው የግልገል ግቤ ፕሮጀክት እንዲህ ሆኖብን ስለከረመ እንደልማዴ የማውቀውንና የሚሰማኝን ላካፍላችሁ መረጥሁ፡ Read more…
አንድነትን ጨምሮ የተቃዋሚ መሪዎች በኔዘርላንድ ኤምባሲ ዉይይት አደረጉ ! አንድነት – ምርጫዉ ነጻና ፍትሃዊ ካልሆነ አልሳተፍም አለ። – ልዩ ዘገባ ከአወደ ኢትዮጵያ
ሰኔ 4 ቀን 2001 ዓ.ም
የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ (አንድነት) ፓርቲ አመራር አባል ኢንጅነር ግዛቸው ሽፈራው፣ የፓርቲው ም/ል ሊቀመንበርና የድርጅት ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ፣ በትናንትናው ዕለት ሰኔ 3 ቀን 2001 ከኔዘርላንድ ከመጡት የሰብአዊ መብት አምባሳደር ከሆኑት፣ ያን ሃምበርገር ጋርና እንዲሁም ከኤምባሲው የኔዘርላንድ አምባሳደርና በኔዘርላንድ ኤምባሲ የልማት ትብብር ክፍል ም/ል ሃላፊ ከሆኑት ጋር ውይይት አካሂደዋል፡፡ Read more…

Recent Comments