ማህደር
በፕሮፌሰር መስፍን የሚመራዉ የዝም አንልሞች ቡድን የአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤትን ሰብሮ ገባ ፤ የመድረኩ የትግራይ ተወዳዳሪ መኖሪያ ቤት ላይ ቦምብ ተጣለ!
አቡጊዳ – ሚያዚያ 20 ቀን 2002
በፕሮፌሰር መስፍን የሚመራዉ የዝም አንልሞች ቡድን አባላት፣ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ዋና ጽ/ቤትን ሰብረዉ ለመግባት በሞከሩበት ጊዜ በተነሳዉ ግጭት በርካቶች እንደታሰሩ ከአዲስ አበባ የደረሰን ዜና ያመለክታል። የዝም አንልሞች ቡድን ዛሬ ሚያዚያ 20 ቀን 2002 ዓም የተዘጋዉን የጽ/ቤቱን በር ሰብረዉ በሚገቡበት ጊዜ የኢትዮጵያ ቴለቭዥን አገልግሎት ባልደረቦች ካሜራቸዉን ጠምደዉ በስፍራዉ ይጠባበቁ ስለነበር በጽ/ቤቱ የታየዉን ሕገ ወጥ ድርጊት እንደቀረጹም ለማወቅ ችለናል። Read more…
በደብረ ብርሃን፣ በደሴ፣ በወልዳይ፣ በኮምቦላቻ እንዲሁም በአዲስ አበባ መብራት ሃይል አዳራሽ ታላላቅ ህዝባዊ ስብሰባዎች ተደረጉ !
አቡጊዳ – ሚያዚያ 18 ቀን 2002
የኢትዮጵያ ፌደራልዊ አንድነት መድረክ በአገሪቷ ክልሎች ሁሉ የሚያደርገውን ሕዝባዊ ስብሰባዎች በመቀጠል በደብረ በርሃን፣ በደሴ፣ በኮምቦልቻ፣ በአዲስ አበባ የመብራት ኃይል አዳራሽ ታላላቅ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ማድረጉን ከስፍራዉ የደረሰን ዜና ያመለክታል። Read more…
ህዝብ የመሆን ጣጣ – ህሩይ አማኑኤሌ /ሉዴስ/
የአቶ ያሬዴ ጥበቡን የቅርቡን የአውራምባ ታይምስ ጋዛጣ ቃለ ምልልስ ሳነብ ሁለት ነገሮች ደጋግመው በአዕምሮዬ ተመላለሱ።
በበለጠ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ!
ክፍት የሐላፊነት ማስታወቂያ! (ከኣባ ቤክሲሳ)
መግቢያ፡
በተለያየ ወቅት ብዙ ወገኖቻችን የተለያየ አቋምና ቅርፅ ባላቸዉ ቡድኖች በመደራጀት በሀገራችን ፓለቲካዊ ለዉጥ ለማምጣት ሲንቀሳቅሱ መቆየታቸዉ ይታወቃል። Read more…
የባሳን ላሞች!! – ዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል
“በሰማሪያ ተራራ የምትኖሩ ድሆችንም የምትበድሉ ችጋረኞችንም የምታስጨንቁ ጌቶቻቸውንም አምጡ እንጠጣ የምትሉ እናንተ የባሳን ላሞች ሆይ ይህን ቃል ስሙ፥ ቅሪታችሁንም በመቃጥን የሚወሰድበት ቀን እነሆ በላያችሁ ይመጣል ብሎ በቅዱስነቱ ምሎአል። እያንዳንዳችሁ በየፊታችሁ በተነደለ ስፍራ ትወጣላችሁ በሬማንም ትጣላላችሁ ይላል እግዚአብሔር።” አሞጽ 4፥1-3 Read more…
መድረኩ ካልተደገፈ ማን ነዉ የሚደገፈዉ ? ምላሽ ለደራሲዉ ማስታወሻ ! – ግርማ ካሳ
ሚያዚያ 16 ቀን 2002 ዓ.ም
«”ከቁጥጥራችን ዉጭ የማይሄድ ፌዴራሊዝምና የምርጫ ሂደት ከተከተልን ለረጅም ጊዜ ትግራይን ስልጣን ላይ ማቆየት ይቻላል» ይላሉ እነ መለስ። ስዬ ከመነሻዉም ይህን ይቃወማል። በዚህ ዘዴ ለረጅም ጊዜ መዝለቅ አንችልም ባይ ነዉ። አማራዉ እስከዛሬ እንደተጠቀመበት ኢትዮጵያዊነት የሚለዉን በሽፋን ተጠቅመን ዉስጥ ዉስጡን ግን የትግራይ ተወላጆችን በሃብትና በእዉቀት በማጠናከር ለረጅም ጊዜ ልንገዛ እንችላለን። አፄ ዮሐንስ ያደጉትን አንደግምም ፤ ስልጣን ከእጃችን ከወጣች ተመልሶ ማግኘት ከባድ ነው“ ይላል ስዬ» Read more…
የኢፕርድፍ ልዑካኖች፦ ብዙ ጥያቅዮችን ይዘው ተመለሱ – በዘውገ ፋንታ (ስያትል)
መግብያ
እሑድ ምያዝያ 18 የኢትዮጵያ ገዥ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣኖች በስያትል ተገኝተው፣ “ከባንክ የተቀመጠ ዕንቁ” ካሏቸው የኢትዮጵያ ወገኖች ጋር የኢትዮጵያን አስከፊ ሁናቴ አስመልክቶ ሰፊ ውይይት አድርገዋል። መልስ ያልተገኘላቸውን ብዙ ጥያቄዎች ልዕካኖቹ ወደ ሀገራችን ይዘው ተመልሰዋል። ትዝብትን ያተረፈ ንግግር ግን ተንጸባርቋል። በጣም ሳይጋነን የምትታወስ ትንሽ የታሪክ ቀን ነበረች ማለት ይቻላል። Read more…

Recent Comments