ማህደር
ይድረስ ለ‹ደኅንነት›ና ‹ፀጥታ› ባልደረቦች በይሄይስ አእምሮ
የደኅንነትና ፀጥታ መጠበቅ ለአንዲት ሀገር ያለው ፋይዳ መኖርንና አለመኖርን በሚወስን መልኩ እጅግ ከፍተኛ ነው፡፡ ለዚህም ሲባል ሁሉም የዓለም ሀገሮች ከውስጥም ሆነ ከውጭ ሊሠነዘሩ የሚችሉ የደኅንነትና የፀጥታ ሥጋቶችን ከወዲሁ ለመከላከልና የመከላከል ደረጃንም አልፈው በእውን ቢከሠቱ ትልቅ ጉዳት ሳያስከትሉ ለማምከን ብዙ ጥረት ያደርጋሉ፡፡ ለዚህ ተግባር ስኬት ሲባልም የደኅንነት(ኢንተሊጀንስ)፣ የፀረ-ደኀንነት(ካውንተር ኢንተሊጀንስ)፣ የምጣኔ ሀብታዊ ደኅንነት (ኢኮኖሚክ ኢንተሊጀንስ) የመከላከያ፣ የፖሊስና ሌሎች የፀጥታ ተቋማትን ገምብተው ከፍተኛ በጀት በመመደብ የሀገርን ድንበርና የሕዝብን ደኅንነት ጥበቃ ያካሂዳሉ፡፡ Read more…
የፍቅር ሐዋርያው ቴዎድሮስ ካሣሁን በፍቅር ይበልጣል
ቃላት እየከዱኝ እንዴት እንደምጅምር ተቸገርኩ፡፡ አንዳንዴ ደስታ ያደርጉትን ያሳጣል፡፡ በተለይማ ደስታና ተስፋ በጠፉበት የጨለማ ዘመን ውስጥ አልፎ አልፎ እንደብርቅ የሚታዩ የሃሤት ምንጮች ሲገኙ በደስታ ብዛት ጮቤ ያስረግጣሉ፡፡ ቴዲ አፍሮ ያደረገውን ስሰማ ጆሮየን ማመን አቃተኝ፡፡ Read more…
የሕወሐት/ኢሕአዴግ ቦንድ ሽያጭ ጥሪ በዳላስ
አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን/ዳላስ ቴክሳስ
በዚህ በያዝነው ሰሞን ከአገርቤት የሚሰማው ሁሉ መልካም ነገር አይደለምና ብዙ ሰው ዳግም ሀዘን ውስጥ ገብቷል። የዚህ ትውልድ ብርቅ ልጆች በመታሰር ላይ ናቸው። አቶ አንዷለም አራጌና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ከሌሎች ጋዜጠኞች ጋር ሆነው ወደ እስር ዳግም ተወርውረዋል። Read more…
ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች በድጋሚ በትላንትናው ዕለት ፍ/ቤት ቀረቡ
“በሽብር” ተግባር ተጠርጥረው ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ከሚገኙት እስረኞች መካከል የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ፓርቲ /ኢብአፓ/ ፕሬዝደንት አቶ ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር፣ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፣ጋዜጠኛ ርዕዮትዓለሙና ወ/ሮ ሂሩት ክፍሌ በትላንትናው ዕለት ፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበዋል፡፡ መዝገቡ ተቀጥሮ የነበረው በክስ አቀራረቡ ላይ የተከሳሽ ጠበቆች ባቀረቡት ተቃውሞ ክሱ እንዲሻሻል ፍ/ቤቱ ብይን በመስጠቱ ነው፡፡ ተሻሽሎ በቀረበውም ክስ በተመሳሳይ ሁኔታ ጠበቆች ቅሬታ በማቅረባቸው ለሁለተኛ ጊዜ በድጋሚ ለብይን ለዛሬ ተቀጥሯል፡፡ Read more…

Recent Comments