በአገራችን ኢትዮጵያ ኢህአዴግ በሥልጣን ላይ በቆየባቸው ባለፉት ሃያ አመታት ውስጥ የተፈፀሙ ኢ-ሠብአዊ፣ ኢ-ዴሞክራሲያዊና ኢ-ፍትሓዊ ድርጊቶችን ስንቃወምና ስናጋልጥ ቆይተናል፡፡ ገዢው ፓርቲ ግን አንድም ጊዜ ስህተቱን ሲቀበልና ሲያርም አልተስተዋለም፡፡ ይልቁንም የተለያዩ አሳሪና አስፈሪ አዋጆችን፣ መመሪያዎችን፣ ድንጋጌዎችን እያወጣና ለሕገ-መንግሥቱ እንኳ ሳይገዛ ባደባባይ በተደጋጋሚ በማን አህሎኝነት ከሕግ በላይ እየሆነ ነው፡፡ ህዝብ በኑሮ ውድነት፣ በመልካም አስተዳደር እጦት፣ በሕግ የበላይነት አለመኖር፣ በሙስና መንሠራፋት፣ በዴሞክራሲያዊ መብቶች አለመከበር ወዘተ በሚደርስበት በደል በየእለቱ ይጮሃል፡፡ ስርዓቱ ግን ‹‹ግመሎችም ይጓዛሉ፤ ውሾቹም ይጮሃሉ›› እንደተባለው ጆሮ ዳባ ልበስ በማለት በድርጊቱ እየገፋበት ይገኛል፡፡ ነገሮች ሁሉ ካቅም በላይ እየሆኑ መጥተዋል፡፡ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) በአገራችን ሠላማዊ የሥልጣን ሽግግር እንዲመጣ አበክሮ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ ፓርቲያችን ለሠላማዊ ትግሉ ባለው ቁርጠኝነት በአዋጅ እስካልተከለከለ ድረስ እስከመጨረሻው ይገፋበታል፡፡ ለዚህም በቁርጠኝነት ይታገላል፡፡ Read more…
ዜና
ተንደርድሬ ጥልቅ ሳልሰናበት ውልቅ ማለት አለመደብኝም እና ወደ ዋናው ጉዳይ ከመግባቴ በፊት የዚህ ሰሞኑ ዜናዎች እንደመክፈቻ ላቋድስ፡፡ ታዲያ ዜና ዘገባው ከተለያየ አቅጣጫ በመሆኑ እና በዛ በማለቱ የዜና አምድ እንዳይመስል ስል አሳጥረዋለሁ ስለዚህ ቅድመ ይቅርታ ላቅርብ፡፡ እለት ከእለት ወደ የመን የሚፈልሰው ስደተኛ ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ እንዳሳሰባቸው ቀይ መሰቀል፣ አይ ኦ ኤም እና በጉዳዩ በጥምረት እየሰሩ ያሉ ድርጅቶች አስታወቁ፡፡ በአሁኑ ሰዓት ከሶማሊያዊያን ይልቅ ይበልጥ እየተሰደዱ ያሉት ኢትዮጵያዊያን መሆንቸውን እና ለጉዳት ተጋላጭ እየሆኑም እንደሆነ ጨምረው አስታውቀዋል፡፡ ጉዟቸው በመረጃ ያልተደገፈ እና ህጋዊ ባልሆነ መንገድ /ህገ-ወጥ/ በመሆኑ ለዘራፊዎች ከመጋለጣቸውም በላይ ለሞት እየተዳረጉ መሆኑንም ድርጅቶቹ አስምረውበታል፡፡ Read more…
ዜና
ሳሊምቢኒ ጥቅምት 1 ቀን፣ 1890 በያዘው ማስታወሻ፣ አጤ ምኒልክ ትግራይ በነበሩ ጊዜ የተፈፀመ አንድ ታሪክ አንስቶአል።
በዚያን እለት ምሽት አጤ ምኒልክ ትግራይ ላይ ከተከሉት ንጉሳዊ ድንኳናቸው ተቀምጠው የቀጠሯትን አንዲት ሴት እየጠበቁ ነበር። እንደተጠበቀውም ማምሻው ላይ ወይዘሪቷ በሁለት አሽከሮች አጀብ በበቅሎ እየሰገረች ከአጤ ምኒልክ ድንኳን ደረሰች። በአካባቢው ብዙ ግርግር አልነበረም። ጥቁር ካባ የደረበች፣ በአበሻ ቀሚስ የደመቀች፣ ጠይም ረዘም ያለች ወይዘሪት ከበቅሎ እንደወረደች በጥድፊያ ወደ ንጉሱ ድንኳን እንድትዘልቅ ተደረገ። ይህች ሴት አልጣሽ ቴዎድሮስ ትባላለች። የአጤ ቴዎድሮስ ሴት ልጅ ስትሆን፣ የአጤ ምኒልክ ደግሞ የመጀመሪያ ሚስት ነበረች። Read more…
ዜና
የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽፈራው ሽጉጤ በከፍተኛ የሙስና ወንጀል እንዲጠየቁ የክልሉ ፓርቲ ባደረገው ድርጅታዊ ግምገማ ውሳኔ አስተላለፈ።
ፕሬዚዳንቱ “እኔ ብቻዬን መከሰስ የለብኝም። ከተከሰስኩም ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ጋር መሆን አለበት” በማለት ስብሰባ ረግጠው መውጣታቸውን ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ ምንጮች አስታወቁ። አቶ መለስ ድርጅቱ የወሰነውን ውሳኔ ቀለበሱ። Read more…
ዜና
የምድር ፈራጅ ሆይ ከፍ ከፍ በል፤
ለትዕቢተኞች ፍዳቸውን ክፈላቸው።
አቤቱ ህዝብህን አዋረዱ፤
ርስትህንም አስቸገሩ።
መዝሙረ ዳዊት 93/4 ቁ 2-5 Read more…
ዜና
ኢትዮጵያዊ ተዋዶ፣ ተዋልዶና ተዛምዶ ኖሯል ለዘላለምም ይኖራል!
እንዳትሰደድ የሚለውን የወዳጅ ዘመድ ምክር ችላ ብለህ ብትሰደድ ከሁሉ በላይ ሕውሓትን አስደስተህ አንተም ይብዛም ይነስም ችግር ውስጥ ለመባዘን ተዘጋጅ። ከዲያስፖራው ወገን ጋዜጠኛ ወይ ባለጠጋ ካልሆንክ ስለተሰደድክ እምቢልታ አይነፋልህም፣ ነጋሪት አይጎሰምልህም። Read more…
ዜና
Recent Comments