ትግል ውጤቱ መራር እና ጣፋጭ ነው፡፡ ጣፋጩን ለማግኘት ከባዱን ጎዳና መጓዝ ግድ ይላል፡፡ እስክንድር ነጋ የታገለበትን ውጤት አዝመራውን አጭዷል፡፡ ከኢትዮጵያ ነፃ-ፕሬስ ጋር ከመጀመሪያው ጀምሮ የታገለ ጋዜጠኛ ነው፡፡ አሁን የወያኔ መንግስት ‹‹አሸባሪ›› የሚል ታፔላ ለጥፎለት በእስር ላይ ቢሆንም ድሉን ማጣጣም የቻለው የፔን ኢንተርናሽናል ሽልማትን ለማግኘት በመብቃቱ ነው፡፡ እሱ በእስር ላይ ቢሆንም ባለቤቱ እና የልጁ እናት ሰርክዓለም ፋሲል ሽልማቱን ተቀብላለች፡፡ እጅግ ደስ የሚል ዜና ስንሰማ ይህ የመጀመሪያችን አልነበረም፡፡ የኢትኦጵ ጋዜጣ አሳታሚ ሲሳይ አጌና አምና ተሸላሚ ነበር፡፡ መንግስት ‹‹አሸባሪ›› ይላል አለም ግን በስራቸው ሽልማት እንደሚገባቸው አምኖ ይሸልማቸዋል፡፡ አለም የተቀበለውን የማይቀበል፣ ሁሉ ያየውን የሚክድ ምን አይነት ቀጣፊ ብድን እንደሆን ኢትዮጵያን የሚያስተዳድራት ማወቅ አቅቷል፡፡ እንደ እስስት መልኩን እየቀያየረ እንደ እባብ ቆዳውን እየሸለቀቀ አጭበርብሮ ማለፍን ተግባሩ አድርጎታል፡፡ Read more…
ዜና
ስፍራው አዲስ አበባ፣ ዘመኑ 1931 ፋሺሽት ኢጣሊያ አገራችንን በሃይል በተቆጣጠረበት ወቅት ነው። አንድ ቀን የወራሪው ጦር አዛዥ የነበረው ማርሻል ባዶሊዮ ግራዚያኒ ሕዝቡን ለማታለልና ለመስበክ “በንጉሳችሁም ሆነ በኢጣሊያ ዘመን የተሰጣችሁ የክብር ልብስ ካለ ለብሳችሁ፤ የተሸለማችሁት ኒሻን ካለም ይህንኑ አድርጋችሁ ነገ ማለዳ ላይ ታላቁ ቤተ መንግስት እንድትሰበሰቡ!” ሲል አዲስ አበባ ውስጥ በራዲዮና በጥሩምባ ያስለፍፋል። Read more…
ዜና
በትግራይ ክልል የልማት ሠራዊት እንዲሆኑ ተብለው የተመደቡ አካላት የወረዳና የቀበሌ አስተዳዳሪዎች በሕወሓት ካድሬ መሪነት ነው እሚንቀሳቀሱት፡፡ የታዘዙትን የሚፈጽሙ ናቸው፡፡ እነዚህ አካላት የተሰማሩበት የሥራ ዓላማ በገጠር በተመረጡ ቦታዎች በመስኖ የሚለማ ግብርና ማፋጠን የሚል ነው፡፡ ለዚህ ተብሎ የታቀደው የልማት አቅጣጫ ደግሞ በተመረጡ የገጠር መንደሮች እያንዳንዱን ገበሬ በእርሻ ማሣው የውሃ ጉድጓድ መቆፈር እንዳለበት ነው፡፡ በተጨማሪ ከደደቢት የብድር ተቋም የውሃ ሞተር በብድር መልክ በመውሰድ ከጉድጓድ ውሃ እየመጠጠ ወደ እርሻ ማሳ እንዲጠያሰራጭ ታስቦ ነው፡፡ ለዚህ ጉዳይ የተመደበው ባጀት እንደሚከተለው ነው፡፡ Read more…
ዜና
Recent Comments